Wednesday, January 19, 2011

እንደምን ከረማችሁ?

ቤተክርስቲያናችንን ከቀበሌ የፍርድ ሸንጎ ወደ ተቀደሰ ደብር ለመለወጥ የተደረገው ጉዞ መልክ እየያዘ መምጣቱ በልዑል አምላካችን ፈቃድና በምእመናኑ ንቁ ተሳትፎ የተገኘ ድል ስለሆነ ሁላችንንም እንኳን ደስ ያለን እንላለን። ስውርና አሳፋሪ የሆነውን ነገር አስወግደናል። በተንኮልም አንሰራም፤ የእግዚአብሔርንም ቃል ከውሸት ጋር አንቀይጥም፤ ይልቅስ እውነትን በይፋ እናስያለን፤ እራሳችንንም በሰው ሁሉ ህሊና ግልፅ እያደረግን በእግዞአብሔር ፊት እንኖራለን።
2ኛ ቆሮንጦስ ቁጥር 4:2 ።
ባለፈው ጽሁፋችን ላይ የቤተክርስቲያናችንን ችግሮች በመጠኑ ለመጠቆም ሙከራ አድርገን ነበር። ችግሮችን ሙሉ በሙሉ ለመፍታት ብቃቱም ሆነ ሥልጣኑ ስለሌለን በዚህች በእኛ ደብር ውስጥ እውነትን በይፋ እያሳየን የእግዚአብሔርንም ቃል ከውሸት ጋር ሳንቀይጥ በፊቱ ለመኖር ቆርጠን ስንነሳ በተቃራኒ ጎራ የነበረውን የሃይል አሰላለፍ አሳውቀናችኋል። ችግሮችን ለመፍታትና ለቤተክርስቲያናችን እድገትን ለማምጣት አስተዋጽኦ ለማድረግ የሚቻለው ግልጽ አሰራር (Transparency) እንዲኖር በማድረግ ነው ብለን ተስማማን።ይህንንም ሃሳብ ከግቡ ለማድረስ አስፈላጊ ናቸው ብለን ያመንባቸውን ነጥቦች በወቅቱ ለነበሩት የአስተዳደር ቦርድ አባላት አቀርብን፤ ከነጥቦቹም ጥቂቶቹ ይሚከተሉት ነበሩ።
1 የቤተክርስቲያኑ የሂሳብ መዝገብ አያያዝ ኋላ ቀር አሰራር ስለሆነ ብዙ ገንዘብ ሲባክን በወቅቱ ለመጠቆምና ለማስተካከል ብቃት አልነበረውም። ስለሆነም በዘመናዊ (Software) ተጠቅመን ማህበርተኛው (On line) በመግባት ወርሃዊ ክፍያውን እንዲከፍል እድል አንዲሰጠውና ያለውንም የገንዘብ እንቅስቃሴ እንዲያይ እንዲደረግ።
2 ማንኛውም የጥገናም ሆነ የቆሳቁስ የግዥ ስምምነት ሲደረግ የአስተዳደር ቦርዱ ህጋዊ ጨረታ እንዲያወጣ፤ አሸናፊ ኩባንያም አሸንፎ የሰራበትን ሰነድ ተቀብሎ ለምእመኑ ባለው የመገናኛ ዘደ ሁሉ እንዲያሳውቅ።
3 የአስተዳደር ቦርዱ ሊቀመንበር የቤተክርስቲያኑን የተለያዩ ኮሚቴወችንና የስራ ዘርፎችን ማስተባበርና መርዳት ካልሆነ በስተቀር ፍጹማዊ የሆነ በግል የፈለገውን የማስፈጸም መብት እንደሌለው እንዲታወቅ።
4 ካህን፤ አስተማሪ፤ ለሌሎችም ክፍት የስራ ቦታዎች ሠራተኛ መቅጠር ቢያስፈልግ፤ “የቅጥር ጊዜያዊ ኮሚቴ” ተቋቁሞ በሚሰጠው ዝርዝር የስራ መመሪያ መሰረት ሶስት እጩወች ለቦርዱ አቅርቦ እንዲቀጠር። 
5 የአስተዳደር ቦርዱ መደበኛ ስብሰባወችን አጀንዳወቹን እያንዳንዱ የቦርድ አባል የሰጠውን ውሳኔ በወቅቱ ለአባላቱ ማሳወቅ። እነዚህን ከላይ የጠቀስናቸው ነጥቦች በወቅቱ ከቀረቡት ሃሳቦች ውስጥ የተወሰዱ ናቸው። ዝርዝሩንም በ (August 26,2009) በዚሁ ገጽ ላይ አውጥተን ነበር። አሁንም ሙሉ ሰነዱን ደግሞ ማንበብ ይቻላል። ዋናው ነገር እነዚህ ሃሳቦች ይህን ያህል አምባ ጓሮና ጭቅጭቅ ማስነሳት ነበረባቸው ውይ?
ውድ ምእመናን ሆይ!
በአምላክ ፈቃድ ዛሬ የደረስንበት ደረጃ ላይ ደርሰናል። ይህንም በጎ ስራ የሰራው የሚወደን አርሱ ራሱ ፈጣሪያችን ነው፤ የሱም መንፈስ በቤተክርስቲያናችን ውስጥ እየጎላ መሄዱን እያሳየን ነው። እናንተ ሸክማችሁ የከበደ ሁሉ ወደኔ ኑ እኔም አሳርፋችኋለሁ እያለን ነው። እኛም ክብሩንና ፀጋውን እንድንጎናጸፍ አስካሁን አውቀንም ሆነ ሳናውቅ የበደልነውን ሁሉ ይቅር በለን! ብለን ወደ ውድ ቤተክርስቲያናችን እንመለስ። ክፉ ልቦናንና ተንኮልንም ይዘን ወደ ደብሩ አንግባ፤ መልካም ተግባርን ለመፈፀምና እርስ በእራስ መዋደድን ይለግሰን ዘንድ ሁላችንም በአንድ ልብ ሆነን እንጸልይ!
አሜን!!

Monday, January 10, 2011

የቤተክርስቲያናችን ችግርች!!!!!

ቀደም ሲል በዚህ ርዕስ ስር መጻፋችን ይታወሳል፤-
ቀን አልፍ ቀን ሲተካ ነገሮች መልካቸውን ለውጠዋል። መሠረታዊ ችግሮች ግን መፍትሄ ሳያገኙ እንዳሉ ይገኛሉ። የቤተክርስቲያናችን መሰረታዊ ችግር የወያኔ መንግስት በቤተክህነት አስተዳደር ውስጥ ጣልቃ በመግባት አመራሩን ሲለውጥ፤ ከገባንበት ቀውስ ውስጥ መውጣት አለመቻላችን ነው።  ዛሬ እንድታነቡት የምንጋብዘው ከላይ የጠቀስነው የጥቃት በትር የራሳችን ደብር ላይ ያደረሰውን
አለመረጋጋት አስመልክቶ የቀረበ አጭር ዘገባ ይሆናል።  ይህ ደብር ሲቆረቆር ቤተክህነት በአንድ ፓትሪያርክ ጥላ ስር ይተዳደር ነበር። ባለንበት ክፍለ ሃጉር በጊዜው የቤተክህነት ተወካይ ሆነው የተሰየሙት ሟቹ አባታችን አቡነ ይስሃቅ ነበሩ። ቤተክርስቲያናችን ተቋቁሞ ሕጋዊ ፍቃድ አውጥቶ የሚተዳደርበትን ሕግ ደንብ አፅድቆ ሲመረቅ በዚህ በዓል ላይ ከተገኙት አባቶች መሃል አንዱ የቀድሞው አባ ጳውሎስ፤ የዛሬው የወያኔ መንፈሳዊ ጉዳዮች ተወካይ አባ ገ/መድህን ነበሩ። እምነታችን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት መሠረት ሆኖ አስተዳደሩ ግን ከሲኖዶሱ ውጭ ራሱን በራሱ የሚያስተዳድር በምእመን የትቋቋመ ደብር መሆኑን የሚገልጽ አንቀጽ
ወጥቶለት በመተዳደርያ ደንቡ ላይ ተካቶ ቤተክህነት የተቀበለችው ሕገ ደንብ አውጥቶ የተቋቋመ ደብር ነው።
ሁላችሁም እንደምታውቁት ወያኔ በቤትክህነት አስተዳደር ውስጥ ጣልቃ በመግባት የመደበውን የመንፈሳዊ ጉዳዮች ተወካይ በተቀበሉና ይህንን አሠራር በተቃወሙ አባቶች ማካከል መከፋፈል ተፈጠረ፤ ይህን ድርጊት አንቀበልም ያሉ አባቶች ሃገር ጥለው ተሰደዱ። በዚህም የቀውስ ሰዓት በምእራብ አህጉራት ውስጥ የሚጠቃለለውና በአባ ይስሃቅ የሚመሩት አብያተ ክርስቲያናት የ እኛ
ደብር ጭምር የተሰደዱትን አባቶች ተቀብለው ማስተናገድና አብረው መስራት ጀመሩ። ዛሬ የ “ውጭ ሲኖዶስ” የሚባለው ተቋቋመ። ከጥቂት አመታት በኋላ አባ ይስሃቅ “ገለልተኛ” ብለው ራሳቸውን አገለሉ። ኢትዮጵያ ውስጥ ደግሞ “ማህበረ ቅዱሳን” ይሚባል ድርጅት ተመሰረተ።
1ኛ፤- የፈራረሱ አብነት ቤተክርስቲያን አድሳለሁ፤
2ኛ፤- ወደሌላ ሃይማኖት የኮበለሉትን ወጣቶች እመልሳለሁ በማለት መንቀሳቀስ ጀመረ።
ክጥቂት አመታት በኋላ በአሜሪካን ሃገር ውስጥ “የምእመናንና የካህናት ጉባኤ” የሚባል ድርጅት ተቋቋመ። በወያኔ የመንፈሳዊ ጉዳዮች ውስጥ ተወልዶ የጎለበተው ማህበረ ቅዱሳን በአጭር ጊዜ ውስጥ ታዋቂና ጠንካራ ድርጂት ሆኖ ወጣ። በቤተክርስትያንም ውስጥ በወያኔ የተፈጠረውን ቀውስ በክፍተኛ ደረጃ እያሰፋ የራሱን ድርጅት ግን እያሳበጠ ሄደ፤ ምእመናኑን ከቤተክርስቲናኑ
እየገነጠለ በድርጂቱ ውስጥ በአባልነት ማደራጀትን ስራ ብሎ ተያያዘ፤ እነዚህኑ ምእመናን ለቤተክርስቲያን የሚከፍሉትን አሥራት አቁመው ለማህበረ ቅዱሳን ድርጂት የአባልነት መዋጮ እንዲከፍሉ አስደረገ። ለቤተክርስቲያኑ ግን በወር አንድ ብር ብቻ መክፈል ተገቢ መሆኑንና ከዚያ በላይ መክፈል እንደማያስፈልግ ማስተማርን ተያያዙት ። መምህራንን፤ ቀሳውስትን፤ጳጳሳትን ቤተክርስቲያን ከምትከፍለው በላይ ድጎማ በመስጠት መቅጠር ጀመረ። ቤተክርስቲያናትን የሚረዳና የሚደግፍ ሳይሆን እራሱን እያሳደገ ቤተክርስቲያንን ይሚያቆረቁዝ ድርጀት ሆነ። የ አባላቱም ታማኝነት ለፈጣሪያቸው አገልግሎታቸውም ለደብራቸው መሆኑ ቀርቶ
ለማህበረ ቅዱሳን ብቻ እንዲሆን አስደረገ።
የዚህን ድርጅት አካሄድ የተረዱትን አባቶች መስደብ፤ ማዋረድ፤ ማሳደድንም እንደሙያ ተያያዙ። ያስተማሩትን ትምህርት እየከለሱና ያላሉትን አሉ በማለት ላልጠበቀ ምእመን በማሰራጨት ህዝቡን አወናበደ። አልፎ ተርፎም ማውገዝ፤ የቅጽል ስም ማውጣትን እንደሙያ ተክኖት ይገኛል። ባህር ተሻግሮ አሜሪካን ድረስ በመምጣት የድርጅቱን አድማስ አስፍቷል። አሜሪካ ውስጥ ደግሞ ተባባሪ ሆኖ ካቋቋመው ሲኖዶስ ውስጥ “ገለልተኛ” በሚል ስም መጥሪያ ራሱን ያገለለው ስብስብ፤ ክዎያኔ መንፈሳዊ ጉዳዮች ተቋም ጋር በሰፊው የስራ መረቡን ዘረጋ። በሩንም ለማህበረ ቅዱሳን ያለግድብ ክፍቶ ድርጂቱ እንዲደራጅ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አደረገ። ማህበረ ቅዱሳንም የገለልተኛ ቤተክርስቲያናትን ገንዘብ ያለቁጥጥር ተጠቀመበት። ሕግና ደንባቸውን ሰብሮ ቤትክርስቲያኖችን ለወያኔ ለመስጠት በቅጥረኝነት ሰራ። ከዳር ሆነው ይህን ሕገወጥ ምዝበራ የተመለከቱ ለጥቅም ያደሩ አባላት እንደማህበረ ቅዱሳን ያለ
የራሳቸው ድርጂት አቋቋሙ።የ “ምእመናንና የካህናት ጉባኤ” ብለው ድርጂታቸውን ሰየሙ። አባታችን አባ ይስሃቅ ከዚህ አለም በሞት ሲለዩ የገለልተኛ ቤተክርስቲያናት ሁሉ ያለ አባት ቀሩ፡ ከላይ የጠቀስናቸው ሁለት ድርጂቶች ቤተክርስቲያኖችን ከ አምልኮት ሥፍራ ወደ ጠላት ስርአት አልባኝነት አሸጋገሯቸው። በተጭማሪም የወያኔ፤ የአማራ ልማት ማህበር (አልማ)፤ ደጀን የፖለቲካ ቡድን እና የ ወ/ሮ አዜብ ጎላ ቤተሰቦች ግንባር ቀደም የጥፋት መልእክተኞች በመሆን ቀን ከሌሊት ይሄው እንደምታዩአቸው በመስራት ላይ ይገኛሉ። በኛ ደብር ውስጥ የተከሰተው ቀውስ በሙሉ በእነዚህ ድርጂቶች አማካኝነት የተሰነዘረ የጠላት፤ የጥፋት ፍላጻወች ናቸው። ከጥፋቶቹ መሃል ጥቂቱን እንመልከት። ማህበረ ቅዱሳን የደብራችን መዘምራን ወደ ኦስተን በመሄድ መቅደስ በመድፈር ሁከት ፈጥሯል። ወደ ዕርቪንግ ማርያም በመሄድ ተመሳሳይ ፅረ ቤተክርስቲያን ስራ ሰርቷል። በእራሳቸን ደብር ውስጥ ሁለት ጊዜ በመደጋገም ፅያፍ ስራውን ፈፅሟል። የማህበረ ቅዱሳን አስተባባሪ የነበረው ዲያቆን ነኝ የሚለው አለማየሁ ደስታ በዘመዱ ያን ጊዜ የቦርድ አባል በነበረው በአቶ ኪዳኔ ምስክር ግፊት የቤተክርስቲያናችን አስተዳዳሪ በነበረት ወቅት ስራውን በገዛ ፍቃዱ ሲለቅ፤
 አንድ፤- የማህበር ቅዱሳን ደጋፊ ነን የሚሉ የቦርድ አባላት፤
 ሁለት፤- የማህበረ ካህናት አባላት የሆኑ መሪዎች በገዛ ፍቃዱ የለቀቀን አስተዳዳሪ ያለምንም ስራ ተዋጽኦ ሳያደርግ ከስድስት ወር በላይ ደመወዝ ከፍለዋል። ከዚህም በላይ የአቶ ኪዳኔ ምስክር የቦርድ አባል ባለቤት የሆኑት ወ/ሮ ጥሩ አየር ፍስሃን እና ሌሎች አባሎቻቸውን በማስተባበር ቤተክርስቲያን ከሰው ሙግት ላይ ይገኛሉ።
አቶ እዮኤል ነጋ የ “ማህበረ ካህናት” ዋና ጽሃፊ ናቸው፤ በሳቸውም ስም የወጣ የዳላስ የ ቀረጥ ነጻ (501.c) ያላቸው በቤተክርስቲያንም ስም ለራሳቸው ገንዘብ ሰብሳቢ የሆኑ ግለሰብ ናቸው።  ባንድ ወቅትም ያውም የቤተክርስቲያናችን ሊቀ መንበር በነበሩበት ወቅት፤ ለዎያኔ የመንፈሳዊ ጉዳዮች ተጠሪ ለ አባ ጳውሎስ የጻፉትን ደብዳቤ ማስነበባችንን አይዘነጋም። አሁንም ደግመው
ማንበብ ይቻላሉ።
ቄስ መስፍንን ማህበረ ቅዱሳን ሲያስቀጥር የአቶ ኢዮኤል ድርጂት ደግሞ ቄስ አወቀ ሲደልልን አስቀጥሯል። ከስራም ሲታገዱ ይህ ድርጂት ህዝቡን ለ ዓመጽ አነሳስቷል። በአሰሪና ሰራተኛ መሃል የተፈጠረውን የአስተዳደር ውሳኔ ማህበረ ቅዱሳን፤ የካህናትና የምእመናን ጉባኤ፤ ከወያኔ ደጋፊዎች ከ ወ/ሮ አዜብ ጎላ ቤተሰቦች ወ/ሮ ፈትለዎርቅ ጎላና ባለቤቷ አቶ ጌታቸው ትርፌ ጋር በመተባበር ቤተመቅደስ ደፍረው ደብሩን የወንጀል ቦታ አድርገው ለማዘጋት የተደረገው ሙከራ በመክሸፉ ሰብአዊ መብት ተረገጠ ብለው ፍርድ ቤት ሄደዋል። የካህናት ማህበርና ይ ወ/ሮ አዜብ ቤተሰቦች ከኋላ ሆነው ይህን ሁሉ ደባ እየሰሩ ዞር ብለው ደግሞ እናስታርቅ በማለት ማወናበድ ላይ ናቸው። ጂራፍ ራሱ ገርፎ ራሱ ይጮሃል የሚባለው አይነት መሆኑን ተረዱ። አመራር ላይ ሆነው ይህን ሁሉ በደል ሲፈጽሙ የነበረውን የአስተዳደር ብልሽት ምእመኑ ተረድቶ ቢያስወግዳቸው በአስታራቂ ሽምግልና ካባ ተጠቅልለው መልሰው ወደ አስተዳደሩ ለመግባት የጀመሩት ሥልት ነው።
በዚህ ጽሁፍ የቤተክርስቲያናችንን ችግሮች ጠቅለል ባለ መልክ ለግንዛቤ ይረዳ ዘንድ አቅርበናል። ይህ ጽሁፍ የወደፊት ቦርድ አባላትን ስትመርጡ በቤተክርስቲያኑ ችግሮች ዙሪያ የሚደረገውን ደባ በቂ ግንዛቤ ካተረፋችሁ የተጀመረው የቤተክርስቲያን የማዳን ርብርቦሽ ላይ ተሳታፊ የሚሆኑ አባላትን ከሰርጎ ገቦች ለይታችሁ ለመምረጥ ያግዛችኋል ብለን ተስፋ እናደርጋለን።
አንዲሁ በንፃ የወደደን ዓምላካችን ማስተዋሉን ያብዛልን፡
አሜን! አሜን! እንበል።