Wednesday, December 22, 2010

የማቴዋስ ወንጌል መራፍ 13/24-30 
መንግሥተ ሰማያት በእርሻው ውስጥ መልካም ዘረን የዘራን ሰው ትመስላለች። ሰወቹ ሲተኙግን ጠላቱ መጣና በስንዴው መካከል ግን እንክርዳድን ዘርቶ ሄደ። ስንዴውም በቀለና ባፈራ ጊዜ እንክርዳዱ ደግሞ ያን ጊዜ ታየ። የባለቤቱም ባሮች ቀርበው ጌታ ሆይ መልካምን ዘር በ እርሻህ ዘርተህ አልነበርህምን አሉት፤- እርሱም ጠላት ይህን አደረገ አላቸው። ባሮቹም እንግዴህ ሄደን ብንነቅለው ትወዳለህን አሉት። እርሱ ግን እንክርዳዱን ስትለቅሙ ስንዴውን ከርሱ ጋር እንዳትነቅሉት አይሆንም። ተዋቸው እስከ መከር ጊዜ አብረው ይደጉ በመከር ጊዜም አጫጆችን፤- እንክርዳዱን አስቀድማችሁ ልቀሙ በእሳትም ለማቃጠል በየነዶው እሰሩ ስንዴውን ግን በጎተራየ ክተቱ እላለሁ አላቸው።”
ውድ የሚካኤል ምእመን ሆይ ዛሬ የቤተክርስቲያናችን ትልቁ ችግር
1 የማህበረ ቅዱሳን
2 የማህበረ ካህናት
3 ከኋላ ሆነው የሚገፏፏቸው የወያኔ መንግስት ደጋፊወችና ጥቅመ ተስፈኞ
4 የክቡር ጠቅላይ ሚኒስተሩ ተቀዳሚ እመቤት ወ/ሮ አዜብ ጎላ ቤተሰብ የሆኑት እነ ወ/ሮ አዜብ፤አቶ ጌታቸው ትርፌ፤ ወ/ሮ ፈትለወርቅ ጎላ፤ናቸው።
እንዚህ ግለ ሰቦች ቤተክርስቲያናቸን ውስጥ የሚጠነስሱትን ማወናበድና ማጋጨት ስንመለከት ከላይ ጌታችን እየሱስ ክርስቶስ ያስተማረው ምሳሌ እንክርዳድ የተባሉት ይሆኑ? የሚል ጥያቄን በአ እምሮአችን መጣ፤
ዛሬ የምናቀርብላችሁ እንግዳ።
የሆለታው ወታደር የነበርው የተፈራ ወርቅና የአቶ በትሩ እንዲሁም የአቶ ኪዳኔ አለማየሁ ግንባር ቀደም ተናካሽ ውሻ በመሆን የዳላስ አካባቢ ተላላኪያቸው አቶ አምሃን ነው።
አኝሁ ግለ ሰብ ከራሺያዊቷ ባለቤታቸው ጋር ወደ ዳላስ ሲመጡ ዶክተር ነኝ በማለት እራሳቸውን አስተዋወቁ። ወዲያውም የማህበር ቅዱሳን ተከታይና አማኝ ነኝ በማለት ቤተክርስቲያናቸን ውስጥ ሰርገው በመግባት የማበጣበጥ ተግባራቸውን ማካሄድ ጀመሩ። ይህን የ! እዩኝ እዩኝ ባህሪያቸውን የተመከቱ ከላይ የተጠቀሱት የጥፋት መሪወች ወደ እነሱ ድርጅት እንዲገቡ አደረጓቸው። በወጣትነታቸውም ለመጠቀም እንዲያመቻቸው መለመሏቸው። ባስቸኳይም ከረሻዊቷ ባለቤታቸው አፋተው ያገራቸው ልጅ የህግ ባለሙያ የሆነች ልጅ ጋር አጋቧዋቸው። እነዚህኑ አዲስ ሙሽሮች ክስንዴው ማሳ ውስጥ እንክርዳድ አድርገው ዘሯቸው። ወዲያውኑም ከማህበረ ቅዱሳን ድርጅት ተገፍተው የወጡ አስመሰሉ። በሌላው በኩል ደግሞ ይሄው የማህበረ ካህናት ድርጅትና ተከታዮች የኢትዮጵያ ኮሙኒቴ ቦርድ እንዲሆኑ አስመረጧቸው። የስራ ዘመናቸውም አልቆ ለሁለተኛው ውድድር ሲቀርቡ እነዚሁ የከተማ አድመኞች እነ አት ኪዳኔ ዓለማየሁ ያለ ምንም ውድድር ያለምንም ድምጽ እንደገና ተመራጭ በማስመሰል ስራቸውን እንዳይለቁ አደረጓቸው። እኝሁ እንክርዳድ፤ ወጣቶች ተደራጅተው በማህበር በማቋቋም፤ በ ኢትዮጵያው ኮሚኒቴ ጥላ ስር እንደባለቅ የሚል ጥያቄ ሲያቀርቡ! የቦርዱ ግንባር ቀደም ተጠሪ በመሆን ድርጅቱ ኮሚኒቴው ውስጥ እንዳይገባ ያስደረጉ ግለ ሰብ ናቸው። የዚህ ደባ መነሻ የሆነው፤ የህግ ባለ ሙያ የሆነችው ባለቤቴ የድርጅቱ መሪ ትሁን በማለት ለጠየቁት ጥያቄ ተቀባይነት ባለማግኘቱ፤ የኔን ባላቤት የበላይነት የማይቀበልም ሆነ በእኛ በ እንክርዳዶቹ ያልታቀፈና ያልተደራጀ ስብስብ ኢትዮጵያ ኮሚኒቴ ወጥ አይገባም በሚል ተንኮልና ማን አለብኝነት የፈጸሙት የእብሪት እርምጃ ነው።
ዛሬም ቤተክርስቲያናችን ውስጥ ክብዙ ሰወች ጋር ተጣምረው ቤተክርስቲያኑ በ ትረስቲ ቦርድ መተዳደር አለበት እያሉ ጸረ ክርስቲያናዊና ተንኮል የተሞላበት እንቅስቃሴ በማድረግ ላይ ይገኛሉ። ለዚሁ ለሚታገሉለት ትረስቲ ቦርድ ያቀረቧቸው ግለሰቦችን ትመለከቱ ዘንድ ዝርዝሩን ይዘንላቹ ቀርበናል።
1 ኪዳኔ አከማየሁ
2 ጌታቸው ትርፌ
3 ተፈራ ዎርቅ
4 በትሩ
5 ግርማቸው
6 ተኮላ
7 ፅሃይ ፅድቅ
7 ደም መላሽ
እና እንደነዚህ የመሳሰሉትን ነው።
እኝሁ ዶ/ር ነኝ ባዩ ግለሰብ ባለፈው ወር ውስጥ ካህናትን እናስታርቅ በሚል ተንኮል ቦርድ ፊት ቀርበው የማህበረ ካህናት ምልምል የሆኑ ቄስ ለማስቀጠር ጫና ሲያደሩ እንደነበረ ባለፈው እትማችን ላይ ስለተዘረዘረ እንደገና ተመልከቱት። ውድ ምእመን ሆይ አሁን ባለው ቦርድ፤ አምባ ገነናዊ ስርአት ተወግዷል፤ የጓደኛነትና
የዘመድነት ግፊትና ጫና ወድቋል፤ በምትኩም መልካም ትብብርና ለደብሩ መልካም ተግባር መፈጸም ተጀምሯል። ባኳያውም መንፈስ ቅዱስ የተመላባቸው መልካም ካህናትን አስተማሪና አስተባባሪዎች አቅርበዋል። እነዚህ እንክርዳዶች ግን መልካሙን ሰብል ለማበላሸት ጧትና ማታ እየታገሉ መሆኑን ተገንዝበን ከመልካሙ ምርት ውስጥ ለቅመን እንድንጥላቸው ቸሩ ፈጣሪ ይርዳን።
አሜን.

Saturday, December 18, 2010

ይህን የመጀመሪያውን ድንጋይ ለመወርወርና ለማስወርወር ግንባር ቀደም ሆነው የተነሱት
የቀድሞው የቦርድ አመራር አባላትና ተከታዮች፦

1 የቄስ ታደሰ ባለቤት ክህኑ ላይ ወዳጅ ይዘው ከቤታቸው በወጡበት ወቅት አንድም ቃል ያልተነፈሱ ናቸው
2 የቤተክርስቲያኑ ገንዘብ በማህበረ ቅዱሳን ሲዘረፍ አብሮ ዘራፊ የነበሩ ናቸው
3 እግዚአብሄር አንድ ያደረገውን ባልና ሚስት ማንም ሰው አንደማይለየው እየታውቀ ለማህበረ ቅዱሳን ይሄድ የነበረው ብር ሲቋረጥ፤ በዛ ተናደው ክስ የሄዱት ውይዘሮ ጥሩ አየርን እየደገፉ “ የከሰሰችው አሷ ነች እኔ አይደለሁም” እያሉ የሚያደናቁሩን
ግለ ሰብ ናቸው፤” ምናልባት ይህ አባባላቸው ው/ሮ ጥሩ አየር ዛሬ ግንባር ቀደም ከሳሽ ተብለው የሚሞገሱት ሴት ከመጀመርያ ባላቸው ተጣልተው ወደ ዳላስ ሲመጡ፤ አቶ ኪዳኔ ምስክር ለሽምግልና ቀርበው ካልጋ እንደወደቁ ያደባባይ ሚስጥር ነው።
ስለዚህ በወዳጅነት የተመሰረተው ይህ ጋብቻ ቀጣይ ዝሙት ስለሆነ አሷ ነች የከሰሰች  የሚለው አነጋገር አለመጋባታቸውን ያሳይ ይሆን? “
4 አቶ መስፍን ወልደየስ በማህበረ ቅዱሳን ስም የወሰደውን መቶ ሰላሳ ሰባት ሽህ ብር ማወራረድ አልቻለም። አሁን ከከሳሾች ጋር አድሞ ብሎግ ክፍቶ አድማ እየመታ የሚገኝ፡ በእግዚብሄር ስም ዳኛ ፊት ቀርቦ ሃሰት የመሰከረ።
5 አት ጸሃይ ጽድቅ (ሰን ሻይን) አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን አገሬ አሰራለሁ ብሎ ከቤተክርስቲያን የውሰደውን ገንዘብ ላባ ጳውሎስ እጅ መንሻ በማቅረብ ከተባረከ በኋላ ተመልሶ ቤተክርስቲያናችንን ለ አባ ጳውሎስ ለማስረከብ በፍርድቤት ክርክር ላይ  ይገኛል;
6 አቶ እዩኤል ነጋ ከላይ የተጠቀሰው የቤተክርስቲያን ካዝና ብዝበዛ ሲካሄድ ምክትል ሊቀ መንበር ሆነው በወንጀሉ የተባበሩና አብረው የመዘበሩ ናቸው። ሊቀ መንበር ሆነው በሚሰሩበት ወቅት፤ በአባ ጳውሎስ ተእዛዝ በአቡነ ቅወስጦስ ጉዳይ
አስፈጻሚነት እና በማህበረ ካህናት አስተባባሪነት ቄስ አወቀ ሲደልልን በሚስጥር  የቀጠሩ ናቸው።
እኝህም ካህን
1 በጾም ወራት ብር ተቀብለው የጋብቻ ስነ ስርአት ሲፈጸሙ፤-
2 እንግዳ ካህን ተጋብዘው መጥተው ሲያስተምሩ አድማ በመምታት ሽንት ቤት ቆልፈው የቅዳሴ ስርአት ሲያሳለፉ፤-
3 በተደጋጋሚ ኪዳን ለማድረስ ስለማይመጡ፤-
4 ቤተመቅደሱ ውስጥ ብጥብጥ ሲያካሂዱ፤ ከ ምእመኑም ሆነ ካስተዳደር ቦርዱ አቤቱታ ሲደርስ ቦርዱ ያስተላለፈውን
የማስጠንቀቂያ ሰነድ ለዚሁ ካህን እንዳይደርስ በተደጋጋሚ የጸደቀውን ሰነድ በመሸሸግ የአሰራር ግዴታቸውን ከ
1 ወ/ሮ ፈትለዎርቅ ጎላ
2 አት ሃይሉ አራጋው ጋር በመተባበር ለተከሳሹ እንዳይደርስ የደበቁ ናቸው። ይህን ሁሉ የማን አለብኝበት ስራ ከፈጸሙ በኋላም የመረጣቸውን አባል ሁሉ ረግጠው ከስራቸው የተሰወሩ ናቸው።
በዚሁ አቶ እዮኤልን በተመለከተ ግፊት ዋና ጸሃፊ ሆነው የሚያገለግሉበትን የማህበረ ክህነት ድርጂት አባሎች
1 አቶ ኪዳኔ አለማየሁ
2 ዶ/ር ሰለሞን አበበ
3 አቶ መሰረት አለነ
4 ዶ/ር ዓምሃን ወ ደ ቦርድ በመላክ፤ የተጣሉ ካህናትን እናስታርቃለን በሚል ዘዴ ሌላ አንደ የቄስ አዎቀ እይነት ካህን እንዲቀጥሩ የቦርዱን ጊዜ በማባከን ጫና ሲያደርጉ ከርመዋል።
8 አት ጊታቸው ትርፌም ክባለቤታቸው ከ ወ/ሮ ፈትለዎርቅ ጎላ ጋር በመሆን ቂስ  ታደሰ የቤተክርስቲያኑን አገልግሎት እለቃለሁ ብለው ሲያመለክቱ፡ ማማልከቻውን ደብቀው ሁለት አመት ሙሉ ያለ አገልግሎት ደመወዝ ሲያስከፍሉ የኖሩ ግለሰብ
ናቸው። ከዝህም በላይ የተጠቀሰው የቤተክርስቲያን ምዝበራና ወንጀል ሁሉ ሲካሄድ እያዩ እንዳላየ በመምሰል በደባው ሲተባበሩ ክመኖርም በላይ ሃሰተኛ ኦዲተር አምጥተው የቤተክርስቲያኑ ሂሳብ ምንም ያልጎደለው ለማስመሰል ሲታገሉና ሲያስፈጽሙ የአደባባይ ሚስጥር ነው። ለቄስ አወቀ ሲደልልም የተጻፈባቸ ማስጥንቀቂያ ሰነድ ሁሉ እንዳይሰጥ ግፊት
ከባለቤታቸው ጋር ሲያደርጉ የኖሩ ናቸው።

እንግዲህ ምእመን ሆይ አሁን ያለው ቦርድ እንደቀድሞወቹ፤ ያወቅሁ የበቃሁ ቅዱስ ነን ብለው አልተመረጡም፤ እንደማንኛችንም ደካማ ግለሰቦች ናቸው። ከነዚህም ተመጻዳቂወች የሚለዩበት ቢኖር
1 ለተመረጡበት የሃላፊነት ስራ ለውሳኔ በሚቀርብላቸው መረጃ መሰረት በህብረት መልካም ውሳኔን ያሳልፋሉ፡
2 ጥፋት ሲያጠፉም ጥፋታቸውን ለመሸፈን አይሯሯጡም፡ ይልቅስ ጥፋታቸውን አምነው መፍትሄ ይሻሉ።
የድሮዎቹ ቦርዶች ክሁዋላ ያሰለፏቸውን የበይ ድርጅቶች በመተው ለቤተክርስቲያኑ በእውነትና በሃቅ ቢሰሩ ኖሮ እዚህ ውድቀት ውስጥ ባልገባን ነበር።
የሁላችንን ለብ የሚያውቀውና የሚመረምረው ፈጣሪያችን መልካም ትምህርቱን እንዳይነፍገን
ጸሎታችንን አናደርሳለን።
ወስብሃተ አምላክ አሜን!

Friday, December 17, 2010

አስቸኳይ መልእክት ለደብረ ምህረት ቅዱስ ሚካኤል አባላት በሙሉ።

አስቸኳይ መልእክት ለደብረ ምህረት ቅዱስ ሚካኤል አባላት በሙሉ።

ቤተክርስቲያናችንን ለማፍረስ ካሁን ቀደም የነበርው ቦርድ ጋር ተጠግተው የቤተክርስቲያኑን ካዝና ሲያራቁቱና ምዕመኑን በዘር፤ በዚጋ፤ በጓደኝነት፤ በአበ ልጅነት፤ በአብሮ ማህበር ጠጭነት ሲከፋፍሉ የነበሩ ግለሰቦችና የድሮው የቦርድ አባላት የሚመለሱበትና አንደገና የሚመዘብሩበት ጥረታቸው በፍርድ ቤት እንዳልተሳካ ስላወቁ አንዳንድ ቀዳዳ እየፈለጉ በሚመጣው ሰንበት እንደገና ቤተክርስቲያን አረከሱ በሚል የተንኮል ተግባር ብጥብጥ አስነስተው ቤተክርስቲያን ሊያዘጉ መዘጋጀታቸውን ልናበስርላችሁ እንወዳለን። እነዚሁ ግለሰቦች ሰሞኑን በቦርዱ ጸሃፊያችን ላይ የደረሰውን አንዳንድ ውዥንብርና አለመግባባት አስመልክተው ገና ያልተፈጸመ ውንጀል ልክ እንደተፈጸመ አድርገው ቤተክርስቲያኑን አሁን ያለው ቦርድ አረከሰ በሚል ሠይጣናዊ ተንኮል በየ ቤቱ እየደወሉና ህዝቡን እያነሳሱ መሆኑን ሁላችንም እናውቃለን።
እነዚህ ሰይጣናዊ አወናባጆች እጃችንን ይዘው ለጥቅማቸው ሲሉ ወደ ገሃነም ሊያስወረውሩን እንጅ እውነት ለቤትክርስቲያኑም ሆነ ለኝ አስበው እንዳልሆነ እንድንረዳ የሚቀጥለውን የአየሱስን ትምህርት የዘንላችሁ ቀርበናል፤ አብረን እናንብበው፦
የዮሃንስ ወንጌል ቁጥር 8/1-11
“-----ጻፎችና ፈሪሳውያንም በምንዝር የተያዝች ሴት ወደ አርሱ አመጡ፤በመካከልም አርስዋን አቁመው፤- መምህር ሆይ ይህች ሴት ስታመነዝር ተገኝታ ተያዘች። ሙሴም እንደነዚህ ያሉት እንዲወገሩ በህግ አዘዘን፤ አንተስ ስለ እርስዋ ምን ትላለህ? አሉት። ---- እየሱስ ግን ጎንበስ ብሎ በጣቱ ብምድር ላይ ጻፈ፤ መላልሰው በጠየቁት ጊዜ ግን ቀና ብሎ ፤-ከእናንተ ኃጢአት የሌለበት አስቀድሞ በድጋይ ይውገራት አላቸው። ድግሞም በጣቱ በምድር ላይ ጻፈ። እነሱም ይህን ሲሰሙ ህሊናቸው ወቀሳቸውና ክሽማግሌወች ጀምሮ አስከ ኋለኞች አንድ አንድ እያሉ ወጡ፤ እየሱስም ብቻውን ቀረ ሴቲቱም በመካከል ቆማ ነበረች። እየሱስም ቀና ብሎ ከሴቲቱ በቀር ማንንም ባላየ ጊዜ፤- አንቺ ሴት እነዚያ ከሳሾችሽ ወዴት አሉ? አላት። እርስዋም ጌታ ሆይ አንድ ስንኳ አለች። እየሱስም፤- እኔም አልፈርድብሽም ሂጅ ከአሁንም ጀምሮ ደግመሽ ኃጢአት አትስሪ አላት።----”
በተጨማሪም፤-
የማርቆስ ወንጌል ቁጥር 7/20-23
“---ከውስጥ ከሰው ልብ የሚወጣ ክፉ አሳብ፤ ዝሙት፤ መስረቅ፤ መግደል፤ ምንዝርነት፤ መጎምጀት፤ ክፋት፤ ተንኮል፤ መዳራት፤ ምቀኝነት፤ ስድብ፤ ትዕቢት፤ ስንፍና ናቸውና ይህ ክፉው ሁሉ ከውስጥ ይወጣል ሰውንም ያረክሰዋል።”
ውድ የቤተክርስቲያን አባላት፤- እንኳን ገና ምንዝር ሲሰራ ያልተያዘ ግለሰብ ቀርቶ ምንዝር በግልጽ ስትሰራ የተያዘችውን ሴት ሳይፈርድባት ሁለተኛ ኃጢአት አትስሪ ብለ ሲያሰናብታት፤ እኛ የትኞቹ ሳድቃን ሆነን ነው የመጀመሪያውን ድንጋይ የምንወረውረው።
በእግዚአብሄር ፊት “ ---ሰውን የገደለንም ሆነ የሰረቀ፤ ምንዝርነት የፈጸመም ሆነ የተዳራ፤ ተንኮል ያዘለም ሆነ የተመቀኘ፤ በሃሰት የመሰከረም ሆነ በሃሰት የከሰሰ ሁሉም” ሃጢአት እኩል መሆኑንና አንዱ ካንዱ ያማይበልጥ መሆኑን ለማሳየት እየሱስ ክርስቶስ ከላይ በማርቆስ ውንጌል ቁጥር 7/20-23 የተናገረውን ተመልሰን እናንበብ።
ታድያ እነዙህ ተንኮለኞች እናንተው ፊት ሲዋሹ፤ በሃሰት ሲመሰክሩ፤ ንጹህ የቦርድ አባላትን ገንዘብ ሰረቁ ብለው በሃሰት ሲከሱ፤ ፍርድ ቤት ቀርበው ወንጌል ጨብጠው ሲቀጥፉ መናፍቃን እይሉ መእመኑን ሲሰድቡ በማርቆስ ውንጌል ቁጥር 7/23 መሰረት የረከሱ አይደሉምን። እኛስ የነሱን የስም ማጥፋትና የማወናበድ ዘመቻ ከተቀበልን መርከስ አይሆንብንም ይሆን? መልሱን ለናንተ ፈጣሪ ልቦናችሁን ከፍቶ እንድታስተውሉት ያደርጋችሁ ዘንድ ምኞታችንን እናቀርባለን። ምናልባት ተሳስታችሁ የመጀመሪያውን ድንጋይ ለመጣል ሳይሆን ለመወርወ ለምትመኙ ሁሉ ይሚቀጥለውን አስቡ። ዋናው ጸሃፊያችን ስራውን ቢለቅ የሚጎዳው ማነው? ቤተክርስቲያኑ ወይስ ጸሃፊው? እንድ የቤተክርስቲያን አገልጋይ ገና ያልተረጋገጠና ያልተፈጸመ ወንጀል አስቧልና ቤተክርስቲያን አያገለግልም ማለት የመጀመሪያውን ድንጋይ መወርወርና በሃሰትም መፍረድ መፍረድ ስለሆነ ከመሳሳታችን በፊት ደግመን ደጋግመን ነገሩን በጥሞና እናሰላስል። የተንኮለኞችን ግፊት ተከትለን
 ን በችኮላ የምናደርገው አድራጎት ግን የሚጎዳው ቤተክርስቲያናችንን አንጅ አገልጋዩን እንዳልሆነም ማመዛዘን አለብን። የህ የተባለው የቤተክርስቲያናችን አገልጋይ አገልግሎቱን ቢያቋርጥ የሚጎድልበት ጉድለት ምን ይሆን?
1 አገልግሎቱን ስላቋረጠ የሚከፈለው ደመወዝ ይቀርበት ይሆን?
2 ከሃገር ይባረር ይሆን?
3 ጊዜውን የሚያሳልፍበት ቦታ ያጣ ይሆን?
4 ሌሊቱን ቤተክርስቲያኑ ለማሻሻል ሲከራከርበት የሚያድርበት ቦታ አያገኝ ይሆን?
5 ወይስ በምንለቅለት ጊዜወች አልጋው ላይ ተኝቶ እንቅልፍ አይወስደው ይሆን?
ባኳያውም ይዚህኑ ግለ ሰብ ቦታ ተክቶ ባስቸኳይ የሚገባ ጻድቅ የሆነ ሰው አዘጋችታችሁ ማቅረብ
ያለባችሁ ግዴታ መሆኑን እንዳትዘነጉ ይሁን። አለበለዚያ የምትበድሉት የራሳችሁን ቤተክርስቲያን
ነው።
በእኛ አስተሳሰብ ወደ ቤተክርስቲያን የሚሄድና የሚጸልይ ብሎም ቤተክርስቲያን አገልግል ትብሎ
የሚጠየቅ ንጽሃን ሳይሆን አውቆም ሆነ ሳያውቅ ሃጢያት የሚፈጽምና አባክህ አምላኬ በደሌን
ይቅር በለኝ አኔም የበደሉኝን ይቅር እል ዘንድ ወደ ፈተናም አታግባኝ የሚል ሁሉ
እቤተክርስቲያን በመድረሱና በመጸለዩ ይቀር ስለተባለ ማንም ሰው ንጽህ ነው።
“እኔም አልፈርድብሽም ሂጅ ከአሁንም ጀምሮ ደግመሽ ኃጢአት አትስሪ አላት” የሚለው
የእየሱስ ጥቅስ ሃጢአት የሰራ ሁሉ ይቅር እንደሚባልና ሃጢአቱም እንደሚደመሰስ ስለሚያስረዳን
ሃጢአትም ሰርቶ የተማረ ሁሉ ንጹህ ነው።
ይሄው ጸሃፊያችን ጥፋት አጥፍቷል ብላችሁ የምታምኑ ካላችሁ መልሳችሁ ክስራው ይባረር
ሳይሆን ንስሃ ይግባ ማለት ብቻ አንጅ በወደቀ ዛፍ ላይ ምሳር ይዞ መረባረብ አይገባም።
በ እግዚአብሄርም ፊትም ሆነ በምድር ያስጠይቃል።
በትዕግስት የአስተዳደር ቦርዱ የሚወስደውን እርምጃ መጠበቅ ግን አግባብ ያለው ይመስለናል።
ለሁላችንም እንደገና የምናመዛዝንበት ልቦና ይሰጠን ዘንድ አምላካችንን እንለምን! 0

አሜን! አሜን!

Tuesday, December 14, 2010

እንዳይፈርድባችሁ አትፍረዱ

እንዳይፈርድባችሁ አትፍረዱ በምትፈርዱበት ፍርድ ይፈረድባችኋልና፤ በምትሰፍሩበትም
መስፈሪያ ይሰፈርባችኋል።
የማቴወስ ወንጌል ቁጥር 7/1

በዚህ በያዝነው ወር በ 13/2010 መረዋ የተባለው የቤተክርስቲያን ክሳሽና ቤተክርስቲያናችንን ላባ ጳውሎስ ለመሸጥ የተዘጋጀው በወያኔው ተዎካይ በ ሻለቃው የተቋቋመው ብሎግ(ጦማር) ስለ አንዱ የቤተክርስቲያናችን አገልጋይ የጻፉትን አንብበን ቆርጠው የተነሱበትን የቤተክርስቲያን ማዘጋት ትግል ለማካሄድ የማይፈነቅሉት ድንጋይና የማይጎረጉሩትን ጉድጓድ እንደሌለ ለማወቅ
አያዳግትም።
“በክርስትና ስምና በኢትዮጵያነታችሁ አሜሪካን አገር ያለውን ቤተክርስቲያን ሁሉ ብትችሉ ለኛ የምታስረክቡበትን ዘዴ ፈልጉ ባትችሉ አዘጉ” ተብለው የተለኩ የቀበሮ ለምድ ለብሰው በውስጣችን የሰረጉ ብዙ ተንኮለኞች እንዳሉ ሁላችንም እናውቃለን። የምንኖረው ህግና ደንብ የሚከበርበት ሃገር ላይ መሆኑን የዘነጉ እነዚህ ተኩላውች፡ አንድ ግለ ሰብ ፍርድ ቤት ቀርቦ ጥፋተኛ ነህ ተብሎ ገና አስታልተፈረደበት ድረስ የነጻነት መብቱ የተጠበቀ መሆኑን በመዘንጋት እንደጥፋተኛ ቆጥረው ማህበርተኛው በከፍተኛ ድምጽ
ብልጫ የመረጠውን የቤተክርስቲያን ነጻ አገልጋይ ከሃላፊነትህ ለማውረድ ቅስቀሳ በማካሄድ ላይ ይገኛሉ።
የዚህኑ የወያኔ ድረ ገጽ ቅስቀሳ ለማንጸባረቅ የምትመኙ ካላችሁ ልናሳስባችሁ ይምንመኘው፦
አንደኛ፤-በምድርም የግለሰብ መብት መግፈፍ ነው።
ሁለተኛ፤- በሰማእታትም “እንዳይፈርድባችሁ አትፍረዱ፡በምትፈርዱበት ፍርድ ይፈረዳችኋልና” ማቴወስ ቁ.7/1
ይሚለውን የየሱስ ክርስቶስን ትዕዛዝ መተላለፍ ነው።
“ታስረው እሑድ ከቤተክርስቲያን መጥተው የምእመናንን ዓይን እያዩ ማስታወቂያ መናገራቸው ቢገርመንም” ለሚለው መልስ በቀላሉ እናንተ ብሆዳችሁ ቂም ይዛችሁ “ዛሬ ምን ይባል ይሆን ቤተክርስቲያን ሄደን ምን እንደሚባል እንሰልል” በማለት ሃይማኖተኛ ለመምሰል የእግራችሁን ጫማ አውልቃችሁ የልባችሁን አሳት ይዛችሁ ወደተቀደሰው ቦታ መግባታችሁን የማያውቅ ም
እመን ይኖር ይሆን?
የጠቀሳችሁት ግለ ሰብ ሊያገለግሉ፤” የመጣውን ምእምን ዓይን እያየ የተናገረው” ላላችሁት አገልጋዩ በሆዳቸው ተንኮል ተሸክመው አለመሆኑን ተረዱ። ጥፋት ቢያጠፉም እንኳን፡ ፈጣሪይቸውን ሰው ነኝና ጥፋት አጥፍቻለሁ ማረኝ። የልቤን እምታውቀው አንተ ነህና ይቅር በለኝ ሳይሉ ወደ መድረክ እንደማይገቡ አንጠራጠርም። አምላካችንም እውነት ጥፋት አጥፍተው እንደሆነ አንደ ማራቸው እናምናለን። የናንተን ትንኮልና መርዝ መርጨት የቤተክርስቲያናችን ምእመን የለመደው ስለሆነ በእናንተ
ተንኮል አይበገርም። ለማለቱማ ድሮ ጀምሮ እኝሁን መልካም አስተዳዳሪ ያላላችኋቸው ስድብና
ዘገባ  ይኖር ይሆን?  
ለዛሬው ይሄን የመርዝ ማለስለሻ ይዘንላችሁ ቀርበናል። 
ሰሞኑን በዝርዝር ተፈጸመ የተባለውን አለመግባባት እስትናቀርብላችሁ ድረስ አወናባጆች እንዳያውናብዷችሁ አደራ እንላለን።
ዋናው መታወቅ ያለበት እኝሁ የተባሉት ግለሰብ ህዝቡ የጣለባቸውን እምነት ለመወጣት ሌት
ተቀን ደከመኝ ክስራ አስተጓጎለኝ ሳይሉ ጉልበታቸውን ጊዚያቸውንና ገንዘባቸውን በነጻ የሚሰጡ መልካም አገልጋያችን ስለሆኑ፤ እንኳን አሉ ባልታ ቀርቶ አዉነት አጠፉ ተብለው  ቢፈረድባቸውም ማስወጣት ቀርቶ ጊዜያቸውንም ሲጨርሱ ካገልግሎት እንዳይወርዱ
የምንማጠናቸው ግለሰብ መሆናቸውን የቤተክርስቲያኑ ምእመን ሁሉም ባንድ ድምጽ ደጋፊያቸው መሆኑን ለጠላቶቻችን እናበስራለን። በ መረዋ ብሎግ ላይ የተፍለጠፈው ተግባር እውነት አለመሆኑን ለመረዳት ከፈለጋችሁ በመጀፍመርያ መጠየቅ ያለባችሁ ነገር ቢኖር መረዋ “የመንገድ ሴተኛ አዳሪ ሲያነሱ ተገኝተው” ያለው የተባለችው ሴተኛ አዳሪ የተነሳችው ለግብረ ስጋ ነው? ወይስ ለሚያካሂዱት የእንጀራ ጋጋሪነት ስራ እንድትሰራላቸው ይሆን? ብሎ ማመዛዘን ተገቢ በሆነ ነበር። በፍርድ ቤት እውነቱ  ውጥቶ እስቲፈርድ ድረስ መታገስን አለመሻት ከዓምላካቸን ጋር እንደሚያጣላን አንጠራጥርም።
የቤተክርስቲያኑ አባላትም ይህንኑ አምኖ ቦርዱ በጊዜው የሚወስደውን እርምጃ በጥሞና
እንዲጠብቅ ጥሪአችን ይድረሳችሁ።
ለሁላችንም አምላካችን የሚያመዛዝን ልቦና እንዲሰጠን እንጸልይ።


አሜን!

Monday, October 18, 2010

ዳግማዊ ክህደት!!!!




የሆለታ 33ተኛው ዙር ምሩቅ የሆኑት ሻለቃ ተፈራ ወርቅ አስፋው በ1966 ዓ.ም. የኢትዮጵያ ህዝብ አብዮታዊ ንቅናቄ ሲያደርግ የኢሃፓ አባል ነበርኩ በማለት ማውራት ይወዳሉ። ደርግ የህዝብን አብዮት ቀምቶ ስልጣን ላይ ሲወጣ ሻለቃው ተገልብጠው የሰደድ አባል ይሆናሉ። ለወታደራዊ ግዳጅ በተሰማሩበት የውጊያ ቀጠና ላይ ደግሞ ከሻብያና ከወያኔ ላይ ብር ተቀብለው ወታደሩ እንዲመታና እንዲበተን ካስደረጉ የጦር መኮንኖች መሃል እንዱ እሳቸው ነበሩ። ህዝብንና ሃገሪቱን ከጠላት ጥቃት እንዲጠብቁ በወታደራዊ ሙያ የሰለጠኑት ሻለቃ የሻቢያና የወያኔ ጦር እየገፋ ሲመጣ በቀውጢው ቀን ሰራዊቱን ክደው ተሰወሩ። ሻለቃ ተፈራ ወርቅ አስፋው ሃገርን ለመክዳት ከሻብያና ከወያኔ ጋር ጦር ሜዳ ለይ ድርድር በሚያደርጉበት ሰዓት ዳላስ ከተማ ውስጥ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ደግሞ

ቤተክርስቲያን ለማቋቋም ይመካከሩ ነበር። የህዝቡም ውይይት ፍሬ አፈራ። በአምላክ ቸርነት በሰሜን አሜሪካ ንብረትነቱ የኢትዮጵያውያን የሆነ የመጀመሪያውና ግንባር ቀደም ቤተክርስቲያን ተከፈተ። በአሜሪካ ውስጥ በተለያዩ ከተሞች ውስጥ ለሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በምሳሌነት የሚጠቅስና ተስፋ ስጭ ደብር ለመሆን በቃ። እንደምታውቁት ወያኔ ስልጣን ላይ ሲወጣ የኢትዮጵያ የመከላከያ ሰራዊት ተበተነ። ጉልበት የነበርውና የተመቸው ወደ ጎረቤት ሃገሮች ተሰደደ። ብዙዎች ታሰሩ፡ አብዛኛው ሰራዊት በሃገሩ ላይ የሚገባበት ቀዳዳ አጣ፡ ተራበ፤ ታረዘ፤ ለማኝ ሆነ። ሻለቃ ተፈራወርቅን በመሰሉ አድር ባዮች ጠቋሚነት አብዛኛው የሰራዊት አባል

በወያኔው ጀኔራል ጻድቃን ትእዛዝ ከተደበቁበት እንደ ድኩላ እየታደኑ ተረሸኑ። ሻለቃ ተፈራወርቅ ግን የወያኔ የዉስጥ አርበኛና ሰላይ ስለነበሩ አዲስ አበባ ከተማ ላይ ዋልያ ኢንሹራንስ ውስጥ ተመድበው እንዲሰሩ ይደረጋሉ። የጦር ባለሙያ ለመሆን የሰለጠኑት ሻለቃ ለወያኔ የሚሳነው የለም በአንድ ቀን ጀንበር የፋይናንስ ባለሙያ ተብለው የኢንሹራንሰ ሰራተኛ ለመሆን በቁ። ካመታት በኋላ የአሜሪካ

መንግስት ዲ.ቪ በሚባል ፕሪግራም ብዙ ኢትዮጵያውያን ማስመጣት ሲጀምር፤ ወያኔም ካድሬዎቹ በዚህ እድል ተጠቅመው ያልቻሉም እጣውን ገዝተው ወደ አሜሪካ እንዲገቡ ያስደርጋል። በሰሜን አሜሪካ ውስጥ ባሉ ቤተክርስቲያናት፤ በኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ማህበራት፤

በእድሮች፤ በእቁቦች፡ በሰንበቴ ማህበራት ውስጥ በአባልነት ተመዝግበው ያመራር ስፍራ እንዲይዙ ባለ ሃምሳ ሁለት 52 ገጽ የስራ መመሪያ ትእዛዝ ወያኔ ይሰጣቸዋል። የዚህ ፕሮግራም ተቀዳሚ ተግባር በውጭ ያሉ የተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅቶችን ለመበተንና ህዝቡን በሙሉ በወያኔ ቁጥጥርና ፕሮግራም መሰረት በሚዋቀሩ ድርጅቶች ውስጥ ብቻ ተሳትፎ እንዲያደርግ ለማድረግ ነው። ሻለቃ ተፈራወርቅ ቀደም ብለው ወደዚሁ ከተማ ከመጡት ባለቤታቸው ጋር ለመቀላቀል ዳላስ ከተማ ሲደርሱ የወያኔ ሰላዮች የኢትዮጵያን ኮሚኒቲ ተቆጣጥረው ስለነበረ እሳቸው ውደዚሁ ማህበር ውስጥ ገብተው ቀደም ሲል በተጀመሩት የወያኔ ድርጅቶች አማካኝነት ህዝቡን ማደንዘዝና ከትግሉ አላማ ህሊናውን የመስለብ ስራ ዉስጥ እንዲሳተፉ ይደረጋል። ሻለቃው የዳላስ ኮሚኒቲ ማህበር ሊቀ መንበር ሆነው

በሚሰሩበት ወቅት የኢትዮጵያ ባህር ሃይል ባልደረባ የነበሩ ወታደሮች ከየመን ወደ ዳላስ ሲመጡ ኮሚኒቲው እርዳታ እንዲያደርግላቸው ሲጠየቅ እኝሁ ሻለቃ ስፖንሰር ሆኖ ላመጣቸው ድርጅት እነዚህን በጥባጭ የባህር ሃይል ወታደሮች ወደ አሜሪካ ማስመጣት አልነበረባችሁም ስህተት ሰርታችኋል በማለት አጥብቀው ሲከራከሩ ነበር። እነዚህም ወታደሮች ዛሬ ዳላስ ውስጥ አሉ። ምስክርነታችሁን ስጡ እንላለን። በዳላስ አካባቢ በወያኔ ካድሬዎች የተዋቀሩ ድርጅቶች የስም ዝርዝር ከዚህ የሚከተለው ነው፡

1 የአማራ ልማት ድርጅት

2 የምእመናንና የካህናት ጉባኤ

3 ሆርን ኦፍ አፍሪካ ደቨሎፕመንት ኤንድ ፒስ

4 ኢትዮጵያን አሜሪካን ቻምበር ኦፍ ኮመርስ

5 ናሽናል አይ ባንክ ኦፍ ኢትዮጵያ

6 ወርልድ አሶሲኤሽን ኦፍ ፓሪሽነርስ ኦፍ ዘ ኢትዮጵያን ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቸርች፡

7 ኢትዮጵያን ኮሙኒቲ ሊደርሽፕ ካውንሰል

8 ደጀን ፖለቲካል ግሩፕ

9 በትሩስ ዩዝ ፕሮግራም በመባል የሚታወቁ ድርጅቶች ናቸው።

እንደምትመለከቱት የኢትዮጵያን ኮሚኒቲ ተቆጣጥረው መጠነ ሰፊ ድርጅቶችን አቋቁመው ጨርሰዋል። በከተማው ውስጥ ያሉትንም ተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጆቶች ደጀን ለዲሞክራሲ በሚባለው ድርጅታቸው ውስጥ በማስገባት እኮላሽተዋቸዋል። ያም በመሆኑ ዛሬ ሃገራችን ላይ ህዝቡ የመምረጥ መብቱን ለማስጠበቅ በሚያደርገው እንቅስቃሴ ላይ አጋር ሆኖ ለመቆም እንዳይችሉ ተደርገዋል። በአንጻሩም እነዚህ የወያኔ ካድሬወች የምእመናንና የካህናት ጉባኤ በሚባለው ድርጅታቸውና በአማራ ልማት ድርጅት እንደዚሁም በማህበር ቅዱሳን አማካኝነት ቤተክርስትያናችንን ለመበተን ባለ ሃይላቸው በመስራት ላይ ይገኛሉ። ሻለቃ ተፈራወርቅ በምእመናንና የካህናት ጉባኤ አማካኝነት ባለፈው የቤተክርስትያን የቦርድ ምርጫ ላይ ተሳታፊ ሆነው ነበር። የወያኔ ካድሬ መሆናቸውን ምእመኑ ጠንቅቆ ስለሚያውቅ ሳይመረጡ ቀሩ። እርሳቸውም እንዲህ ያለ ሽንፈት እንዲደርስብኝ ያደረገው በደጀን የፖለቲካ ደርጂት ዉስጥ ያቀፍኩት የኢህአፓ ድርጅት ነው ብለው ማስወራቱን በአደባባይ ተያያዙት። እንግዲህ በስውር ስሠራ የነበረው ስራ በህዝቡ ዘንድ ከታወቀ በይፋ መንቀሳቀስ አለብኝ ብለው ወሰኑ። የዳላስ ቅዱስ ሚካኤል ደብር መላከ ሳህል አወቀ ሲደልል የሚባሉ በዲፕሎማት ፓስፖርት የሚንቀሳቀሱ ያባ ጳውሎስ ካድሬ ካህን የሆኑትን ክስራ ሲያሰናብት ሻለቃ ተፈራወርቅ አስፋውና አቶ በትሩ ገ/እግዚአብሄር በነገሩ ዉስጥ ጣልቃ በመግባት አስር ሰው የሚገኝበት ኮሚቴ አቋቋሙ። በዚህ ኮሚቴ ውስጥ አቶ ተኮላ መኮንን እና አቶ ሃይሉ እጅጉ የሚባሉ ግለ ሰቦች በአባልነት ይገኙበታል። ደብሩን ለወያኔ ለመስጠት ካልሆነም ለመበተን ቀን ክሌት በመስራት ላይ ይገኛሉ። ይህ ደብር ሲመሰረት እነዚህ ሁለት ካድሬወች ኢትዮጵያ ውስጥ ህዝብ ሲያደሙ ነበር። ደብሩን ለማቋቋም ድንቡሎ ያልከፈሉ ሰወች ተልኳቸው ሃገርና ህዝብን መበተን ስለሆነ ዛሬም ዳግማዊ ከህደት ላይ ተሰማርተዋል። እዲስ ባቋቋሙት ኮሚቴ አማካኝነት የሚከተሉትን ስራወች ሰርተዋል።

1 ቤተክርስትያን ውስጥ በተደጋጋሚ ጊዜ ርብሻ አስነስተው መቅደስ አስደፍረዋል

2 ቤተክርስትያኑን የሚከስ ቡድን አቋቁመው በገንዘብ እየረዱ ይገኛሉ

3 ጉባኤ ጠርተው ተጨማሪ ኮሚቴ አቋቁመዋል። በዚሁ አዲስ ኮሚቴ ውስጥ ሻለቃው በድጋሜ ተመርጠው ገብተዋል።

4 በ 05/17/10 ዓ.ም. ፎክስ ቴለቪዥን (Channel 4 news) የውሸት ፕሮግራም እንዲቀርብ አስተባብረዋል።

ወደፊት እነዚህ የወያኔ ካድሬወች የሚሰሩትን ተንኮልና ስራ እየተከታተልን እናቀርባለን።

እግዚአብሄር ጽናትና ሃይሉን እንዲሰጠን እንጸልይ። አሜን!!

Wednesday, August 18, 2010

እንደምን ከረማችሁ?


ቤተክርስቲያናችን ላይ የተፈጥረው ችግር በሚካኤል ረዳትነት እየተዳከመ ይገኛል ። ህዝቡን በመንፈሳዊ ትምህርት ሊመግቡ የሚችሉ መምህራን እየተጋበዙና በቋሚነትም ተመድበው እያስተማሩት የገኛሉ። በዚህም ምክንያት በየሳምንቱ ወደ ቤተክርስቲያኑ የሚመጣው ያማኝ ቁጥር እየበረከተ መሄዱን ሁላችንም የምናየው ሃቅ ነው። በአንጻሩም ይሀን መልካም ተግባር ለማፍረስ ታጥቀው የተነሱ የጥፋት መልእክተኞች ሌት ተቀን በመደራጀት ላይ ይገኛሉ። ይህንንም ጉዳይ በተመለከተ በጃችን ላይ ያለውን መረጃ ይዘንላችሁ ቀርበናል፤ አብረን እናንብበው።
Selam W/o Fetelework.
Last time at your place we had a good productive discussion.
The Diner was very nice and I was happy with you that night.
Thank you for the Information, I already updated the phone Information on my phone book.
Talk to you soon.

Teferawork Assefa(Tefe)
GASHA Insurance Agency
11420 E Northwest HWY Suite 97
Dallas, TX 75218-1418
(BP)214-420-6000
(CP)214-682-3929
(BP)1-877-278-3104
(BF)214-242-6741
www.gashainsurance.com 
Reply Forward

Friday, June 25, 2010

ለ (June 26 2010) ዓ.ም ስብሰባ የጠራው የአማራጭ ፈላጊ ኮሚቴ በሁለት ቡድን ተከፈለ!!! 
ከእናንተ አንዱ ክርስቲያን ከሆነው ወንድሙ ጋር ቢጣላ፣ ጉዳዩን የእግዚአብሔር ሰዎች በፍርድ እንዲያዩለት በማድረግ ፈንታ ለክስ ወደ አረማውያን የፍርድ ሸንጎ ለመሄድ እንዴት ይደፍራል? 1ኛ ቆሮ፡ 6፡1 
ታዲያ አንድ ክርስቲያን ሌላውን ክርስቲያን ከሶ ወደ አረማውያን ፍርድ ቤት መውሰድ ይገባዋልን? 1ኛ ቆሮ፡ 6፡6
August 18 2009 ዓ.ም
1 ከአገር ቤት በመጡ ንቡረእድ                  4 አቶ መስፍን ወልደየስ
2 አቶ ጌታቸው ወ/ሚካኤል                       5 አቶ ኪዳኔ አለማየሁ 
3 አቶ በቀለ ተክሌ                                  6 ወ/ሮ ጥሩአየር ፍስሃ
አማካኝነት በሰላምና በእርቅ ስም የተዋቀረው ኮሚቴ አንዴ የሰላም፤ የሽማግሌ፤ የእርቅ፤ አማራጭ ፈላጊ ኮሚቴ የሚል የተለያየ ስም እየተሰጠው በተለያየ ወቅት አባላቱን እየቀያየረ አዲስ ሃሳብ ያመጣ ለማስመሰል ቀደም ሲል የቀረበውን ሃሳብ እየለዋወጠ በተለያዩ ፍርድ ቤቶች ውስጥ አዲስ ክስ እየመሰረተ ይገኛል።
June 26 2010 ዓ.ም በጠሩት ስብሰባ ላይ
1 የዝህን ቡድን ስውር ደባ ውለው አድረው በተረዱና ከኮሚቴው ውስጥ ለመውጣት በወሰኑ የአመራር አባላት ምትክ ጉዳዩ በግልጽ ያልገባቸውን አድስ ሰዎች ለማስመረጥ
2 የአስተዳደር ቦርዱ ሊያነጋግረን ፈቃደኛ ስላልሆነ ለዚህ መፍትሄው ሌላ ክስ መስርቶ ቤተክርስቲያኑን ውጥረትና ኪሳራ ላይ ለመጣል የገንዘብ መዋጮ ማሰባሰብ ግንባር ቀደም አጅንዳቸው ነው።
ዉድ ምእመን ሆይ!
የአስተዳደር ቦርድ እንዚህ መጠነ ስፊ ስም ያላቸው ኮሚቴዎች እንደሚያስወሩት ምእመንን አላነጋግርም ያለበት ወቅት የለም። ቀደም ሲል አባል ከሆኑ ከኮሚቴው ተወካዮች ጋር በተደረገ ስብሰባ ላይ ቦርዱ ለመታረቅ ያቀረበው ሃሳብ የሚከተለው ነው።
1 ውይይት ለመጀመር ከሳሾች ክሳቸውን ያንሱ!
2 ቤተክርስቲያን ለክሱ ያወጣቸውን ገንዘብ ይተኩ!
3 ፍርድ ቤት ከሰው ያቀረቡትን ምእመን ይቅርታ ይጠይቁ የሚል ነበር።
በነዚህ ስመ ብዙ ቡድኖች በኩል የቀረበው ሃሳብ ደግሞ፡
1 ክሱን ለማቆም ወደ ፊት እንደራደራለን፡
2 ቤተክርስቲያኑ ለክሱ ያወጣውን ገንዘብ ቤተክርስቲያን የሚመጣ ማንኛውም ኢትዮጵያዊ እንደ አባል ተቆጥሮ ድምጽ ይስጥበት፡
3 ክሱን ለማቆም በጊዜው የነበረው ቦርድ ወርዶ በውጭ ስወች ሞግዚትነት መተዳደር አለበት
4 አዲስ የቦርድ ምርጫ መደረግ አለበት።
5 አዲሱ ህግ ተሽሮ በድሮው ህግ መተዳደር አለበት።
6 ቤተክርስቲያን መጥቶ የሚሳለም ሰው በሙሉ እንደ አባል ተቆጥሮ ድምጽ የመስጠት መብት ይሰጠው። የሚሉ ነጥቦች ነበሩ። ውይይቱ ወደፊት ያልሄደው ከላይ በተጠቀሱት ነጥቦች ምክንያት እንጅ ኮሚቴወቹ እንደሚያናፍሱት ወሬ ቦርዱ አልወያይም ያለበት ጊዜ የለም።
ይህ ደብር የዚህ ሃገር መንግስት በሚፈቅደው ህግ መሰረት የተቋቋመ የራሱ መተዳደርያ ደንብ ያለው ቤተክርስቲያን ነው። በየጊዜው የሚመረጡ የአስተዳደር ቦርድ አባላት የመተዳደርያ ደንቡ በሚፈቅደው መሰረት መስራት ግዴታቸው ነው። አሁን ያለው አስተደአደር ቦርድም ከመተዳደሪያ ደንብ ውጭ የሰራው ስራ ካለ አባላት የመጠየቅ መብታቸው በዚሁ ህግ ላይ በማያሻማ ሁኔታ ሰፍሮ ይገኛል።
እውነቱ ይሄው ነው።
የሃሰት እድሜ አጭር ነው። እውነት ግን ለዘላለም ትኖራለች። ምሳሌ 12:19
 ወዳጄ ሆይ! ደጉን ምሰል እንጂ ክፉውን አትምሰል። ደግ ስራ የሚሰራ ሁሉ የእግዚአብሔር ነው። ክፉ ስራ የሚሰራ ግን እግዚአብሔርን አላየውም። 3ተኛ የዮሓንስ መለክት ቁጥር 11

Wednesday, June 23, 2010

እንደምን ከረማችሁ?

እንኳን ለአመቱ የሚካኤል ንግሠ በአል አደረሳችሁ!
የሰሞኑን አጫጭር ዜናወች እናቀርብላችኋለን። 
ሰብተምበር 25 2009 (September 25, 2009) ላይ የሽማግሌን ኮሚቴ በአዲስ መልክ ለማዋቀር ጅምሩ ቀጥሏል በማለት መጻፋችን አይዘነጋም። ይሄው ኮሚቴ (June 22, 2009) ዓ.ም ላይ በዳብለትሪ ሆቴል ተሰባስቦ ያዋቀረው ኮሚቴ አንደኛ ዓመቱን አከበረ። ለበዓሉም ድምቀት ይሰጠው ዘንድ “ የዓርብ ጉባዔ በአዲስ መልክ ተጀመረ፡፡ ብለው በደብራችን አጠገብ በሚገኘው የኬንያውያን ቤተ ክርስቲያን ላኛው አዳራሽ ውስጥ ስብሰባ ጀምረዋል”።
አቶ ሃይሉ እጅጉ ይሄንኑ የኬንያውያን ቤተክርስቲያን ገዝቼ ለዚሁ ቡድን እሰጣለሁ ሲሉ ተሰምቷል። ቤተክርስቲያኑንም በቅዱስ ሚካኤል ስም እንደሚሰይሙት የደረሰን ዘገባ ይጠቁማል። እኝህ በፍትዎኦት እና በንዋይ ልባቸው የታወረ ግለሰብ ለዝና እና ለርካሽ ወሬ ካልሆነ በስተቀር ገንዘብ ያወጣሉ ተብሎ አይጠበቅም።
ታዛቢዮች ይህ ደርጊት፤ለአቶ ሃይሉ እጅጉ ከመድሃኔአለም ት/ቤት ባሻገር የነበረችውን የጉለሌዋን የቡና ቤት እመቤት እና የቦሌዋን ወ/ሮ ጽጌን እስከነ ልጃቸው የመደባለቅን ያህል ቀላል ታስክ(Task)እንደማይሆንላቸው ይገምታሉ። እኛ በበኩላቸን ግን መልካም እድል እንመኝላቸዋለን።
ሁላችሁም እንድምትመለከቱት ግልጽ እየሆነ የመጣው የቀድሞው የቦርድ አባላት እና ክኋላ ሆነው ችግሩን ሲገምዱ የነበሩት አቶ ጌታቸው ትርፌና ቤተሰቦቻቸው ግንባር ቀደም የኮሚቴው መሪ ሆነው መቅረባቸው ነው። ቤተክርስቲያን ላይ ፐቲሽን አልፈርምም ብለው ሲገዘቱ የነበሩት ወ/ሮ አዜብ ዛሬ ግንባር ቀደም አስፈራሚ ናቸው።
አቶ ሃይሉ አራጋውም ደጀ ሰላም ውስጥ በግልጽ ሽማግሌ ጠልፈው ለመጣል ውንጀል ሲፈጽሙ ታይተዋል። ከዛም አልፈው በሚካኤል በዓል ላይ የድምጽ ማጉያውን ለማበላሸት ሲሯሯጡ ብዙ ምእመን አይቶ ታዝቧቸዋል። የገንዘብ መቀበያ ኮምፒተሩንም እንዳበላሹት መረጃ አለ። በነጻ ለበረከት ተብሎ ለሚሰጥ ግልጋሎት ቦታውን አለቅም ብሎ አምባጓሮ መፍጠርን ምን አመጣው?
በሌላ በኩል ሰሞኑን ከተማችኝ ውስጥ ወደ ኢትዮጵያ ለሚተላለፍ TV እርዳታ ለመሰብሰብ ጉባኤ መደረጉ ይታወሳል።
የሆለታው ሻለቃ ተፈራ ወርቅ በዚህ ስብሰባ ላይ አልተገኙም ነበር።ስራቸው ኢትዮጵያን ማድማት የኢትዮጵያ የሆኑትን ተቋማት ማፍረስ ስለሆነ ለ June 27 2010 ሚካኤልን ለማፍረስ በጠሩት ስብሰባ ቀድመ ዝግጅት ለማደረግ ጎንበስ ቀና ሲሉ ጊዜ አጥሯቸው እንደሆነ ይገመታል።
ለዛሬው በዚህ ይብቃን! 
ቸር ይግጠመን! አሜን!

Friday, June 11, 2010

ቤተክርስቲያናችን ወደት እየሄደች ነው?
ይህንን ጥያቄ የጠየቁት ወ/ሮ አዜብ ኅይለማርያም ናቸው። ወ/ሮ ፈትለወርቅ ጎላ በምርጫ በተሸነፉበት ጌዜ ለወዳጆቻቸው በሙሉ ያቀረቡት ጥያቄ ነበር። ጊዜም ሳያጠፉ በምርጫው ከተሸነፍን አበራን እና ዶ/ር ግርማን ሌባ ብለን ወንጅለን ህዝቡን በማስቆጣት አነሳስተን ያቀረቡትን ሪፖርት እንኳን ለምእመኑ ሳያቀርቡ ለማባረር ተብሎ በተቀነባበረው ሴራ ውስጥ ያጣሪ ኮሚቴ ሆነው ገቡ። በዚህ ኮሚቴ ውስጥም አቶ ኪዳኔ ምስክር አብሯቸው እንዲገቡ የጠቆሙት እኝህ ወ/ሮ ነበሩ። አቶ ኪዳኔ ምስክር ከባለቤታቸው ከወ/ሮ ጥሩአየር ፍስሃ ጋር ቤተክርስቲያንን የከሰሱ፤ የዲያቆን አለማየሁ አጎትና የቦርድ አባል በነበሩበት ወቅት ወደ ሃያ ሽህ የሚጠጋ ብር ከቤተክርስቲያኑን የዘረፉ ናቸው።
ወ/ሮ አዜብና አቶ እዮኤል ነጋ አዴስ የተመረጡትን የቦርድ አባላት የተተራመሰውን ቦርድ መስመር እስከምናሲዝ ድረስ ስራቸውን እንዳይጀምሩና የድሮዎቹ እንዳሉ እንዲቀጥሉ ለማድረግ ያደረጉትን ጥረት ማን ይዘነጋዋል? ጥረታቸው መክሸፉን ሁላቸንም ያየነው ጉዳይ ነው።
ቄስ ነኝ የሚለው አወቀ ሲደልል በሰራው ሃጢያት ከቤተ ክርስቲያን ሲባረር ቤተክርስቲያን ላይ ሁከት የፈጠረው ቡድን
1  የወያኔ ድርጅት መስራች የሆኑት ያቦ ጸሃየ ቤተሰብና የሟቹ የትግራይ ልማት ድርጅት ሃላፊ እህቶች
 ሀ   ወ/ሮ  የሽ ዘሪሁን
 ለ   ወ/ሮ  ሶፊያ ዘሪሁን
2     የወያኔው መሪ  የአቶ መለስ ባለቤት ወ/ሮ አዜብ መስፍን ጎላ ቤተሰቦች
ሀ    ወ/ሮ   አዜብ ኅይለማርያም
ለ    አቶ   ጌታቸው ትርፌ
3   ማህበረ ቅዱሳን
4    የወያኔ አባላት እና ደጋፊወች እንደነበሩ ሁላችንም እናስታውሳለን።
ሚካኤል በጥበቡ ይህንን ደባ ሲያከሽፍ ወደ ፍርድ ሸንጎ ተሯሩጠው ነጎዱ። በየቦታውም ጸረ ቤተክርስቲያን ስብሰባወች አካሄዱ። ቤተክርስቲያን የማዘጋት ህልማቸውም ከሸፈ።
ወ/ሮ  አዜብ ግን ትግላቸውን በመቀጠል
1    አቶ   እዮኤል ነጋ   ከእግዚአብሄር ቤት በገዛ ፍቃዱ የኮበለለ፤
2    ወ/ሮ  ፈትለወርቅ ጎላ፤
3    አቶ  ሃይሉ አራጋው   በውሸት ብዛት ምላሳቸው የተቆለፈ፤ በቴፕ ሲቀዱ የነበረውን የቤተክርስቲያን ሰነድ እስከዛሬ ያላስረከቡ፤
4    ሻምበል  ግዛው ገድሉ   ከማህበረ ቅዱሳን ጋር በመሆን ብዙ መቶ ሽህ ብር በላይ ቤተክርስቲያኒቱን ያራቆተ፤
5    አቶ   ኪዳኔ ምስክር  ከባለቤታቸው ጋር የቤተክርስቲያን ከሳሽና ብዙ ገንዘብ ያባከኑ፤
6    አቶ ጌታቸው ትርፌ   ከቀድሞው ቦርድ ጀርባ በመሆን ለደረሰው ጥፋት ሁሉ ግንባር ቀደም አማካሪና አስተባባሪ። ሃሰተኛ ኦዲተር ለቦርድ አቅራቢ፤
7   ሻለቃ ተፈራወርቅ   ቤተክርስቲያኑን የሚከሱና የሚወነጅሉ ሽማግሌዎች ነን የሚሉ ያባ ጳዉሎስ ተወካዮች ግንባር ቀደም አስተባባሪ። አሁንም እንሸመግላለን ስብሰባ ለማድረግ ፐቲሸን አለኝ ብለው ማቅረብ አቅቷቸው June 27 ስብሰባ የጠሩ በዛ ላይ የሚገኘውን ሰው ስም ዝርዝር  ይዘው ለመቅረብ በዝግጀት ላይ ያሉ፤
8   አቶ በትሩ  ቤተክርስቲያኑን የሚከሱና የሚወነጅሉ ሽማግሌዎች ነን የሚሉ ያባ ጳዉሎስ ተወካዮች ጋር የሚዶልቱ፤
ለአብነት ስማቸው ከላይ የተጠቀሱትን ግለሰቦች ከነባለቤቶቻቸው በማስተባበር በህግ የተቋቋመውን ቦርድ አዉርደው ሌላ ቦርድ ለመመስረት በመሯሯጥ ላይ ይገኛሉ።
የመሪነቱን ቦታ አንለቅም ተብሎ ይሄ ሁሉ ትግልና መሰሪነት የሚካሄደው እውነት  ለቤተክርስቲያን ደህንነት ታስቦ ይሆን ወይስ ሌላ የተሸፈነ አጀንዳ ይኖር ይሆን? እና ወ/ሮ አዜብ ቤተክርስትያናችንን ወዴት እየወሰዱት ነው?
መልሱን ለናንተ ለውድ ቤተክርስቲያን ወዳጆች እንተዋለን።
አምላካችን ለቤተክርስቲያናቸን የሚበጀውን ተግባር ይለግሰን አያልን ጸሎታችንን አናቀርባለን።
አምላክ በቸርነቱ ከዚህ ሁሉ ፈተና ያድነን።
ሁላቸንንም ለንስሃ ያብቃን
አሜን! አሚን1 አንበል!!!!!

Monday, May 17, 2010

ዳግማዊ ክህደት!!!!

የሆለታ 33ተኛው ዙር ምሩቅ የሆኑት ሻለቃ ተፈራ ወርቅ አስፋው በ1966 ዓ.ም. የኢትዮጵያ ህዝብ አብዮታዊ ንቅናቄ ሲያደርግ የኢሃፓ አባል ነበርኩ በማለት ማውራት ይወዳሉ። ደርግ የህዝብን አብዮት ቀምቶ ስልጣን ላይ ሲወጣ ሻለቃው ተገልብጠው የሰደድ አባል ይሆናሉ። ለወታደራዊ ግዳጅ በተሰማሩበት የውጊያ ቀጠና ላይ ደግሞ ከሻብያና ከወያኔ ላይ ብር ተቀብለው ወታደሩ እንዲመታና እንዲበተን ካስደረጉ የጦር መኮንኖች መሃል እንዱ እሳቸው ነበሩ። ህዝብንና ሃገሪቱን ከጠላት ጥቃት እንዲጠብቁ በወታደራዊ ሙያ የሰለጠኑት ሻለቃ የሻቢያና የወያኔ ጦር እየገፋ ሲመጣ በቀውጢው ቀን ሰራዊቱን ክደው ተሰወሩ። ሻለቃ ተፈራ ወርቅ አስፋው ሃገርን ለመክዳት ከሻብያና ከወያኔ ጋር ጦር ሜዳ ለይ ድርድር በሚያደርጉበት ሰዓት ዳላስ ከተማ ውስጥ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ደግሞ
ቤተክርስቲያን ለማቋቋም ይመካከሩ ነበር። የህዝቡም ውይይት ፍሬ አፈራ። በአምላክ ቸርነት በሰሜን አሜሪካ ንብረትነቱ የኢትዮጵያውያን የሆነ የመጀመሪያውና ግንባር ቀደም ቤተክርስቲያን ተከፈተ። በአሜሪካ ውስጥ በተለያዩ ከተሞች ውስጥ ለሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በምሳሌነት የሚጠቅስና ተስፋ ስጭ ደብር ለመሆን በቃ። እንደምታውቁት ወያኔ ስልጣን ላይ ሲወጣ የኢትዮጵያ የመከላከያ ሰራዊት ተበተነ። ጉልበት የነበርውና የተመቸው ወደ ጎረቤት ሃገሮች ተሰደደ። ብዙዎች ታሰሩ፡ አብዛኛው ሰራዊት በሃገሩ ላይ የሚገባበት ቀዳዳ አጣ፡ ተራበ፤ ታረዘ፤ ለማኝ ሆነ።  ሻለቃ ተፈራወርቅን በመሰሉ አድር ባዮች ጠቋሚነት አብዛኛው የሰራዊት አባል
በወያኔው ጀኔራል ጻድቃን ትእዛዝ ከተደበቁበት እንደ ድኩላ እየታደኑ ተረሸኑ። ሻለቃ ተፈራወርቅ ግን የወያኔ የዉስጥ አርበኛና ሰላይ ስለነበሩ አዲስ አበባ ከተማ ላይ ዋልያ ኢንሹራንስ ውስጥ ተመድበው እንዲሰሩ ይደረጋሉ። የጦር ባለሙያ ለመሆን የሰለጠኑት ሻለቃ ለወያኔ የሚሳነው የለም በአንድ ቀን ጀንበር የፋይናንስ ባለሙያ ተብለው የኢንሹራንሰ ሰራተኛ ለመሆን በቁ። ካመታት በኋላ የአሜሪካ
መንግስት ዲ.ቪ በሚባል ፕሪግራም ብዙ ኢትዮጵያውያን ማስመጣት ሲጀምር፤ ወያኔም ካድሬዎቹ በዚህ እድል ተጠቅመው ያልቻሉም እጣውን ገዝተው ወደ አሜሪካ እንዲገቡ ያስደርጋል። በሰሜን አሜሪካ ውስጥ ባሉ ቤተክርስቲያናት፤ በኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ማህበራት፤
በእድሮች፤ በእቁቦች፡ በሰንበቴ ማህበራት ውስጥ በአባልነት ተመዝግበው ያመራር ስፍራ እንዲይዙ ባለ ሃምሳ ሁለት 52 ገጽ የስራ መመሪያ ትእዛዝ ወያኔ ይሰጣቸዋል። የዚህ ፕሮግራም ተቀዳሚ ተግባር በውጭ ያሉ የተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅቶችን ለመበተንና ህዝቡን በሙሉ በወያኔ ቁጥጥርና ፕሮግራም መሰረት በሚዋቀሩ ድርጅቶች ውስጥ ብቻ ተሳትፎ እንዲያደርግ ለማድረግ ነው። ሻለቃ ተፈራወርቅ ቀደም ብለው ወደዚሁ ከተማ ከመጡት ባለቤታቸው ጋር ለመቀላቀል ዳላስ ከተማ ሲደርሱ የወያኔ ሰላዮች የኢትዮጵያን ኮሚኒቲ ተቆጣጥረው ስለነበረ እሳቸው ውደዚሁ ማህበር ውስጥ ገብተው ቀደም ሲል በተጀመሩት የወያኔ ድርጅቶች አማካኝነት ህዝቡን ማደንዘዝና ከትግሉ አላማ ህሊናውን የመስለብ ስራ ዉስጥ እንዲሳተፉ ይደረጋል። ሻለቃው የዳላስ ኮሚኒቲ ማህበር ሊቀ መንበር ሆነው
በሚሰሩበት ወቅት የኢትዮጵያ ባህር ሃይል ባልደረባ የነበሩ ወታደሮች ከየመን ወደ ዳላስ ሲመጡ ኮሚኒቲው እርዳታ እንዲያደርግላቸው ሲጠየቅ እኝሁ ሻለቃ ስፖንሰር ሆኖ ላመጣቸው ድርጅት እነዚህን በጥባጭ የባህር ሃይል ወታደሮች ወደ አሜሪካ ማስመጣት አልነበረባችሁም ስህተት ሰርታችኋል በማለት አጥብቀው ሲከራከሩ ነበር። እነዚህም ወታደሮች ዛሬ ዳላስ ውስጥ አሉ። ምስክርነታችሁን ስጡ እንላለን። በዳላስ አካባቢ በወያኔ ካድሬዎች የተዋቀሩ ድርጅቶች የስም ዝርዝር ከዚህ የሚከተለው ነው፡
1 የአማራ ልማት ድርጅት
2 የምእመናንና የካህናት ጉባኤ
3 ሆርን ኦፍ አፍሪካ ደቨሎፕመንት ኤንድ ፒስ
4 ኢትዮጵያን አሜሪካን ቻምበር ኦፍ ኮመርስ
5 ናሽናል አይ ባንክ ኦፍ ኢትዮጵያ
6 ወርልድ አሶሲኤሽን ኦፍ ፓሪሽነርስ ኦፍ ዘ ኢትዮጵያን ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቸርች፡
7 ኢትዮጵያን ኮሙኒቲ ሊደርሽፕ ካውንሰል
8 ደጀን ፖለቲካል ግሩፕ
9 በትሩስ ዩዝ ፕሮግራም በመባል የሚታወቁ ድርጅቶች ናቸው።
እንደምትመለከቱት የኢትዮጵያን ኮሚኒቲ ተቆጣጥረው መጠነ ሰፊ ድርጅቶችን አቋቁመው ጨርሰዋል። በከተማው ውስጥ ያሉትንም ተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጆቶች ደጀን ለዲሞክራሲ በሚባለው ድርጅታቸው ውስጥ በማስገባት እኮላሽተዋቸዋል። ያም በመሆኑ ዛሬ ሃገራችን ላይ ህዝቡ የመምረጥ መብቱን ለማስጠበቅ በሚያደርገው እንቅስቃሴ ላይ አጋር ሆኖ ለመቆም እንዳይችሉ ተደርገዋል። በአንጻሩም እነዚህ የወያኔ ካድሬወች የምእመናንና የካህናት ጉባኤ በሚባለው ድርጅታቸውና በአማራ ልማት ድርጅት እንደዚሁም በማህበር ቅዱሳን አማካኝነት ቤተክርስትያናችንን ለመበተን ባለ ሃይላቸው በመስራት ላይ ይገኛሉ። ሻለቃ ተፈራወርቅ በምእመናንና የካህናት ጉባኤ አማካኝነት ባለፈው የቤተክርስትያን የቦርድ ምርጫ ላይ ተሳታፊ ሆነው ነበር። የወያኔ ካድሬ መሆናቸውን ምእመኑ ጠንቅቆ ስለሚያውቅ ሳይመረጡ ቀሩ። እርሳቸውም እንዲህ ያለ ሽንፈት እንዲደርስብኝ ያደረገው በደጀን የፖለቲካ ደርጂት ዉስጥ ያቀፍኩት የኢህአፓ ድርጅት ነው ብለው ማስወራቱን በአደባባይ ተያያዙት። እንግዲህ በስውር ስሠራ የነበረው ስራ በህዝቡ ዘንድ ከታወቀ በይፋ መንቀሳቀስ አለብኝ ብለው ወሰኑ። የዳላስ ቅዱስ ሚካኤል ደብር መላከ ሳህል አወቀ ሲደልል የሚባሉ በዲፕሎማት ፓስፖርት የሚንቀሳቀሱ ያባ ጳውሎስ ካድሬ ካህን የሆኑትን ክስራ ሲያሰናብት ሻለቃ ተፈራወርቅ አስፋውና አቶ በትሩ ገ/እግዚአብሄር በነገሩ ዉስጥ ጣልቃ በመግባት አስር ሰው የሚገኝበት ኮሚቴ አቋቋሙ። በዚህ ኮሚቴ ውስጥ አቶ ተኮላ መኮንን እና አቶ ሃይሉ እጅጉ የሚባሉ ግለ ሰቦች በአባልነት ይገኙበታል። ደብሩን ለወያኔ ለመስጠት ካልሆነም ለመበተን ቀን ክሌት በመስራት ላይ ይገኛሉ። ይህ ደብር ሲመሰረት እነዚህ ሁለት ካድሬወች ኢትዮጵያ ውስጥ ህዝብ ሲያደሙ ነበር። ደብሩን ለማቋቋም ድንቡሎ ያልከፈሉ ሰወች ተልኳቸው ሃገርና ህዝብን መበተን ስለሆነ ዛሬም ዳግማዊ ከህደት ላይ ተሰማርተዋል። እዲስ ባቋቋሙት ኮሚቴ አማካኝነት የሚከተሉትን ስራወች ሰርተዋል።
1 ቤተክርስትያን ውስጥ በተደጋጋሚ ጊዜ ርብሻ አስነስተው መቅደስ አስደፍረዋል
2 ቤተክርስትያኑን የሚከስ ቡድን አቋቁመው በገንዘብ እየረዱ ይገኛሉ
3 ጉባኤ ጠርተው ተጨማሪ ኮሚቴ አቋቁመዋል። በዚሁ አዲስ ኮሚቴ ውስጥ ሻለቃው በድጋሜ ተመርጠው ገብተዋል።
4 በ 05/17/10 ዓ.ም. ፎክስ ቴለቪዥን (Channel 4 news) የውሸት ፕሮግራም እንዲቀርብ አስተባብረዋል።
ወደፊት እነዚህ የወያኔ ካድሬወች የሚሰሩትን ተንኮልና ስራ እየተከታተልን እናቀርባለን።
እግዚአብሄር ጽናትና ሃይሉን እንዲሰጠን እንጸልይ። አሜን!!

Friday, May 14, 2010

የኢትዮጵያው ፓትሪያርክ አባ ጳውሎስ የሚካኤልን ደብር በግድም ይሁን በውድ በቁጥጥራቸው
ስር ለማድረግ የማያወላውል ትእዛዝ አስተላለፉ!!
ውድ የቅዱስ ሚካኤል ደብር አባላት በሙሉ!! እንደምን ከረማችሁ?
ፓትሪያርክ ጳውሎስ ወደ አሜሪካን ከላኳቸው እና እዚህም ከመለመሏቸው ካህናት ጋር በ05/12/10 ዓ.ም. ምሽት የቴሌ ኮንፈረንስ (Teleconference) ማድረጋቸው ተረጋገጠ። ከዳላስ ከተማ የስብሰባው ተሳታፊ ከነበሩት መሃል ዋና ዋናዎቹ ፦
1 መነኩሴ ታደሰ አርአያ (ቄስ ታደሰ አርአያ) በሚል መጠሪያ የሚታወቁ- ከባለቤታቸው ጋር  ለአመታት ተጣልተው ተለያይተው ስለነበረ በህገ ቤተክርስቲያን መሰረት ቅስናቸውን ያፈረሱ ሲሆኑ፤ ባለቤታቸውም የጴንጤ ሃይማኖት ተከታይ ናቸው።
· (ሀ) ዘረኛ በመሆናቸው ቤተክርስቲያንን ጥለው የወጡ
· (ለ) በወያኔ ድጋፍ ተክለሃይማኖት/አቡነ አረጋዊ የሚባል ቤተክርስቲያን ያቋቋሙና የሚመሩ።
2 ርእሰ ደብር ሞገስ እጅጉ በ2006 ዓ.ም. በቤተክርስትያናችን ታሪክ ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ ሁከት አስነስተው ምእመኑን እርስ በራሱ አጣለተው ቤተክርስትያንን ለሁለት የከፈሉ፦
 ለዚህም ስራቸው የገንዘብ ድጋፍ ከአቶ ሃይሉ እጅጉ የተቀበሉ
 ባሁኑ ሰአት በአባ ጳውሎስ ስር የሚተዳደር የቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስትያን መሪ፦ 
3 መላከሳህል አወቀ ሲደልል፦ ደብራችንን ለአባ ጳውሎስ ለመስጠት ባደረጉት እንቅስቃሴ ከቤተ ክርስትያናችን የተወገዱ፦
 ሻለቃ ተፈራወርቅ አሰፋ
 አቶ በትሩ ገ/እግዚአብሔር
አቶ ተኮላ መኮንን
አቶ ሃይሉ እጅጉ፤ የተባሉ ግለሰቦች የሚገኙበት አስር ሰዎችን ያዋቀረ ኮሚቴ አቋቁመው የትግል ጓደኛቸው ርእሰ ደብር ሞገስ እጅጉ እንዳደረጉት፤  ሁለተኛውን ዙር የቤተክርስትያን ሁከት ያቀነባበሩ፡
ለአምስተኛ ጊዜ ቤተክርስትያናችን ላይ የተፍከፈተውን ክስ ከአቶ ሃይሉ እጅጉ በተገኘ  ገንዘብ አቶ ተኮላ መኮንንና አቶ ጸሃይ ጽድቅ ቤተማርያም በተባሉ ግለሰቦች በኩልእያስፈጸሙ ያሉ፤
 በቅርቡም ሌላ አዲስ ኮሚቴ አቋቁመው ደብሩን ለማፍረስ እየተንቀሳቀሱ የሚገኙ ሲሆን።
በቴሌ ኮንፈረንሱ ላይ የወያኔው ፓትሪያርክ ለውይይት ካቀረቧቸው አጀንዳወች መሃል አንዱ ስለ ዳላስ ቅዱስ ሚካኤል ደብር ነበር።
በዳላስ አካባቢ የተመደቡት ካድሬ ካህኖቻቸው በአንድነት መቆም ሲገባቸው በግል ጥ ቅምና ዝና እየተጠላለፉ ዌር ሃውስ (Ware house) ውስጥ ጥቃቅን ቤተክርስትያናት መክፈታቸው እንዳሳሰባቸው ክገለጹ በኋላ ይህም አሰራር ህዝቡን በአንድ ጥላ ስር አሰባስቦ ለመግዛትና ለማራቆት አመች ስላልሆነ በዚህም ምክንያት ራሳችሁን እንኳ ችላችሁ ለመቆም የገንዘብ እጥረት ችግር ደርሶባችኋል። ስለዚህ፦
1 በመሃላችሁ ያለውን ቅራኔ ባስኳይ አስወግዳችሁ ተቻችላችሁ በአንድነት እንድትሰሩ ፡ 
2 ውህደት ካደረጋችሁ በኋላ በህብረት ሚካኤልን በእኔ በትረ ስልጣን ስር  እንድታዉሉ። ለዚህም ስራ የሚያስፈልገውን ማንኛውንም ወጭ እንደሚልኩ ቃል ገብተዋል።
3 በእርሳቸው ስር የሚተዳደሩት በአሜሪካ ዉስጥ ያሉ አብያተ ክርስቲያናት በሙሉ በዚህ ትግል ላይ በሚቻላቸው ሁሉ ትብብር እንዲያደርጉ አዘዋል።
ውድ ምእመናን ሆይ! ይህ በሚቀጥሉት ጥቂት ቀናት ውስጥ የሚጀመር አዲስ እቅድ ስለሆነ ቤተክርስቲያናችንን ነቅተን መጠበቅ አለብን።
ተግተን ወደ እግዚአብሄር እንጸልይ!!

Tuesday, May 11, 2010

የሌባ አይነ ደረቅ! መልሶ ልብ ያደርቅ!!!!

ውድ ምእመናን ሆይ! እንደምን ከረማችሁ? የዳላስ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስትያን ሲመሰረት የነበራችሁ ሰዎች እንደምታስታውሱት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን መንበሩ አዲስ አበባ ላይ ሆኖ በአንድ ፓትሪያርክ ስር ይተዳደር ነበር። ዛሬ የምናየው ክፍፍል ባልነበረበት ሰዓት ላይ የተቆረቆረው ደብራችን በመተዳደርያው ደንብ ( By Law) ላይ ቁልጭ ብሎ እንደተጻፈው፦
1ኛ፦ እምነታችን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት መሰረት የሚከናወን ሲሆን

2ኛ፦ አስተዳደሩ ደግሞ ከአባል ምእመናን ውስጥ በሚመረጡ የቦርድ አባላት እንደሚፈጸም ይደነግጋል።

Monday, May 10, 2010

ቅዱስ ሚካኤል በሰይፉም ባይሆን በተአምሩ ቤቱን እየጠበቀ መሆኑን ሳንገነዘብና ሳናመሰግን አናልፍም።

የቅስና ልብስ ለብሰው ለ ሶስት ዓመት ያህል ምንም የማናውቀውን ምእመን እርስ በርስ ሲያፋጁን የኖሩት ቄስ ሚካኤል በታምሩ የገላገለን መሆኑን የሰማነው ቆየት ያሉ ቀናትም ቢሆኑ በርግጠኛ መታወቁን ዩ ቱበ ላይ ዛሬ ስላገኘን እናንተም እንድታዩት አድራሻዉን ይዘንላችሁ ቀርበናል።
http://www.youtube.com/watch?v=b3cNpId8BYQ.
ወይም ዩ ቱበ ሄዳችሁ የሚቀጥለውን ብትጽፉ ያመጣላችኋል;
mahber kidusan and woyane in dallas
ለወደፊቱ ቦርድ ለምን እንደወጡ ሲያስረዳን ያደርጉት የነበረውን ኢ-ክርስቲያናዊ ድርጊቶች
በዝርዝር እናቀርባለን።

Friday, April 30, 2010

የቄስ መስፍን ደምሴ ከቅዱስ ሚካኤል ስንብት!

እንደምታውቁት ቄስ መስፍን ደምሴ ባለፈው እሁድ መጽሃፍ ቅዱስ ለአማኙ ምእመን ለማስተማር ወጥተው የእየሱስ ክርስቶስና የመላእክት ስም የሚነሳበትን የቅዳሴ መድረክን ላይ የራሳቸውን እሮሮ እየዘረዘሩና ህዝቡን ለማራበሽ አይዟችሁ እያሉ ግብረአበሮቻቸው እንዲተባበሯቸው ጥሪ ሲያደርጉ አርፍደዋል። እኝህ አባት ቄስን የሚሾመው “ እግዜአብሄር እንጅ ሌላ ቄስ ወይም እግዜአብሄር በምስሉ የፈጠረው ስው አይደለም” ባሉበት አንደበታቸው በጥቂት ደቂቃ ውስጥ ያሉትን ዘንግተው ራሳቸውን ከባትሪ ጋር አመሳስለው ባትሪዬ አለቀ ብለው አሉ። እኔ የማስተምረው እዉነቱን የእግዚአብሔርን ቃል ነው በማለትም ተናገሩ። ታዲያ የባትሪዉን ማለቅ የማን ቃል ብለን እንውሰደው።
ቄስ መስፍን ደምሴ የማህበረ ቅዱሳን አባል ናቸው። ቅስና ሰጥቷቸው የሾማቸውና እኛ ቤተ ክርስትያን ላይም የመደባቸው ይሄው ማህበረ ቅዱሳን ነው። ቄስ መስፍን ለምን ራሳቸውን ከስራ ለማሰናበት ወሰኑ ብለን ብንጠይቅ? መልሱን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጥቅላይ ጽ/ቤት በ ቀን 27/01/2009 ዓ.ም በቁጥር ል/ጽ/55/2002 ያስተላለፈውን ውሳኔ ላይ ልናገኝ እንችላለን።
በ ገጽ 6 በማህበረ ቅዱሳን አባላት ላይ በማደራጃ መምሪያው የቀረበ ክስ እንጠቅሳለን “በአጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት በወረዳ ቤተ ክህነትና በሃገረ ስብከት ሥራ ጣልቃ እየገባ ምስጢሩ ያልገባቸውን ንጹሓን ወጣቶች በማነሣሣት ሰላም የሚነሣ ችገር እንዲፈጠር ማድረጉ፤” “ማህበሩ በኢትየጵያ ቅዱስ ሲኖዶስ ሥር ሆኖ መንቀሳቀስ ሲገባው በውጭ ዓለም ከሚገኙ ትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስና የቅዱስ ፓትርያርኩን አመራር ከማይከተሉ አባላት ጋር ሆኖ በመስራት ላይ የሚገኝ መሆኑ፤” በማለት ላቀረበው ክስ የተሰጠውን መመሪያ በ ገጽ 12 ላይ እንደገና እንጠቅሳለን “ 1. ማህበሩ ከዛሬ ጀምሮ ግንኙነቱ በመተዳደሪያ ደምቡ መሠረት ከሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ጋር ብቻ ይሆናል፤ ከመምሪያው እውቅና ውጨ የሚፈጽመው ክሦስተኛ ውገን ጋር ግንኙነት ሕገ ወጥ መሆኑን እንዲገነዘብ፤” በማለት ውሳኔ በመሰጠቱ ምክንያት;- የሚካኤል ቤተክርስቲያን በአባ ጳውሎስን የማይቀበል በሲኖዶሱ የማይተዳደር ገለልተኛ ቤተክርስትያን ስለሆነ የቄስ መስፍን በሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ማገልገል ህጋዊና አግባብ አይደለም። ይህንኑ ተረድተው የወሰኑት ውሳኔ ነው ብለን እንገምታለን።
ሌላው ተአምር መላከ ሳህል አወቀ ሲደልል ባጠፉት ጥፋት ሲባረሩ የሚካኤልን ተአምር ያዩት ቄስ መስፍን እንዳሰቡት የሚካኤል ቤተክርስቲያን የቆመው ለምእመኑና ገለልተኛ እንጅ ለማህበረ ቅዱሳን አለመሆኑን ስለተረዱና የተጠነሰሰው ደባ ሁሉ እየከሸፈ መሄዱን በመመልከት በምንም ተአምር የሚካኤል ቤተክርስቲያን ለአባ ፓውሎስ እንደማይሄድ ስለተረዱ ነው።ሆኖም ግን በመጨረሻ ሰአትም ቢሆን በሰላም ከመሰናበት ይልቅ የተለመደውን የማህበረ ቅዱሳን ዘዴ በመጠቀም ህዝቡን ለማበጣበጥ ያቀዱት ሴራ ከሽፏል።
ውድ ምእመን ሆይ የማህበረ ቅዱሳን አባል የሆኑት ቄስ መስፍን ደምሴ እውነተኛ ቄስ ቢሆኑ ኖሮ እላይ እንደጠቀስነው ስጋውንና ደሙን ለሰው ለጅ የሰጠው የእየሱስ ክርስቶስ ስም በሚጠራበት መድረክ ላይ ቆመው የግል እሮሯቸውንና (call to arms) ጥሪ ባላደረጉ ነበር።
ይጅወትንና የልብወን አምላክ ይስጥልን ከማለት በቀር ሌላ የምናደርገው ነገር ስለሌለ ዛሬ በዚህ እንሰናበታለን።
ሃያሉ አምላካችን ቤተክርስቲያናችንን ከማናውቀው ጠላት ይጠብቅልን፤
አሜን!--

Wednesday, April 28, 2010

የደጀን ለዲሞክራሲ አንጃዎች በዳላስ ሚካኤል ላይ ጥቃት እየሰነዘሩ ነው!!!!

ደጀን ለዲሞክራሲ የሚባለው የዳላስ የፖለቲካ ፎረም ከፍተኛ የአመራር አባላት ከ 04/25/10 ዓ.ም ጀምሮ ጸረ ቤተክርስቲያን ሰብሰባ እያደረጉ መክረማቸው ታወቀ። ሰብሰባውን የሚመሩት የደጀን ለዲሞክራሲ ከፍተኛ የአመራር አባላት፤-

1 የሆለታው ሻለቃ ተፈራወርቅ አሰፋ
2 አቶ በትሩ ገ/እግዚአብሔር የተባሉ ግለሰቦች ናቸው።

ይህንን ሰብሰባ በጅ መርጠው ከጠሯቸው ግለ ሰቦች ጋራ ማድረጋቸው ታውቋል። በዚህ ሰብሰባ ላይ ከተሳተፉት ግለ ሰቦች መሃል፤-

1 መላከ ሳህል አወቀ ሲደልል (በቅርቡ ከስራ የተሰናበቱ)
2 ቄስ መስፍን ደምሴ (04/25/10 ዓ.ም ምእመን ፊት ለማሰተማር ቀርበው ወንጌል ከማስተማር ይልቅ በመቅደሱ መድረክ ላይ ቆመው የስንብት ንግግር በማደረግ ሥራቸውን በፍቃዳቸው መልቀቃቸውን ያወጁ)
3 አቶ ተኮላ መኮንን (የወያኔ የአማራ ልማት ድርጅት አባል፤ቤተ ክርስቲያንን የከሰሱ ቡድኖች ግንባር ቀደም ደጋፊ በመሆን ሁልጊዜ ፍርድ ቤት የሚቆሙ፤ ብዙ ህዝብ አስተባብሬ የሚካኤል አባል እንዳይሆኑና ብር እንዳይሰጡ እስተባብሬአለሁ እያሉ የሚመጻደቁ፤
ባይሎው ለውጨ ላባ ጳውሎስ ካላስረከብኩ ብሎ የሚታገሉ፤ በአሁኑ ሰዓት ቦዘኔ የሆኑ LOOSER) እነዚህን የመሳሰሉ ገለሰቦች ይገኙበታል።

እነዚህ አንጃ የደጀን አመራር አካላት በ04/25/10 ዓ.ም ቄስ መስፍን የስንብት ንግግር አደርገው እንዳበቁ፤ ለቡራኬ ሳይቀርቡ ጸበል ስይቀምሱ በሆለታው ሻለቃ መሪነት ተከታትለው ክቤተክርስቲያን ዉስጥ በመውጣት ፓርኪን ሎት ላይ ተገናኝተው ሲመካከሩ ታይተዋል። የጥቃቱን መጀመርያ ዱላ እንደ ሪሞት ኮንትሮል ኦፍ ኤንድ ኦን በሚያደርጉት የሬድዮ ሰራተኛቸው በአቶ ዘውገ ቃኘው አማካኝነት፤ ጸጥታ ለማስከበር ቤተክርስቲያን በተገኙ ፓሊሶች ላይ የተዛባ ሃተታ በማቅረብ ከፈቱ።

ላዛሬ እንድታውቁት የምንፈልገው እነዚህ ግለ ሰቦች የኢትዮጵያን ኮሙኒቲ ራዲዮ ተገን በማድረግ ቤተክርስቲያን ላይ ደባ መጀመራቸውን እና በየቦታው ስብሰባ እያካሄዱ መሆናቸውን እንድትረዱ ነው።
ወደፊት የስብሰባቸውን አጀንዳና የነዚህን አንጃ ወዶ ገብ ወያኔዎች የህይወት ታሪክ እናቀርብላችኋለን።

ፈጣሪያችን ከነዚህ ሃያላን ፍላጻ እንዲጠብቀን እንጸልይ!
አሜን! አሜን! እንላለን።

-

Friday, April 23, 2010

እንደምን ከረማችሁ!!
 ይህን ግጥም አብረን እናንብብ።
            ማነህ አንተ የቅርባችን እሩቅ?
            እኛማ እኛ ነን ያንተስ ከየት ይሆን?
            ያስተሳሰብህ መደቡ? ማነህ አንተ?
            ሳጥናኤል ነህ ከንቱኤል? ዳንኤል ነህ ዋሾኤል?
           “ጋሼ!” በሉኝ የምትል፤የአዛውንት ቅምጥል፤
           ያለባበስና የንግግር ሊቅ! የት ነህ አንተ የቅርባችን ሩቅ?
           ሆደ ባሻ ነህ! ወንድም ውሻ? ወንድም ጋሻ ነህ የተስፋ እርሻ?
          ባለ ራእይ ነህ ወይስ ተልካሻ?
                   እባክዎ “እርሶ” ማኖት አንቱ? እውነቱ ወይስ ክህደቱ?
                  ቃሎት የሆነብን ከንቱ? ማኖት እርሶ?
                  ለተስፋና ለፍቅር፤ ፍጻሜው ሆነብን እንጂ - ቃል ብቻ የቃል ክምር!
                  አንተኛውስ ማነህ?
        ጆሮጠቢ ነህ የገንዘብ ወፍጮ?
        መቀጮ ነህ ወይስ መዋጮ?
       ማነህ አንተ? ማነሽ አንቺ? የት ነሽ አንቺ?
       እና እኔ ደግሞ ለማን እንደሆነ ባላውቅም!
       “እባክህ ማነህ አንተ?” ብዬ ጠየቅሁ።
                እንደሆዱ ነህ እንዳንጎሉ? የት ነው ያስተሳሰብህ ክልሉ?
                የራእይ ኮከብ ቃሉ? የት ነው? ማነህ አንተ? የት ነህ አንተ?
                ምነው የህሊናህ ባንዴራህ ተደበቀ?
               ምነው ክብርህና ኩራትህ ተሳቀቀ?
    ማነህ አንተ? ጀብደኛ ነህ ቀልደኛ? ወይስ ተመጻዳቂ ህልመኛ?
    እና የት ነህ አንተ? ማነህ አንተ? ወንድም ውሻ? ወይስ ወንድም ጋሻ? 
                                           ከደራሲ ተስፋየ ገብረአብ የተወሰዱ ግጥሞች።

Friday, April 16, 2010

የቤትክርስትያናችን ችግሮች!! 

የቤተክርስቲያናችንን ችግሮች በተመለከተ ዛሬም ይዘን ቀርበናል። የቤተክርስትያን አባላት የሆኑት አቶ ኪዳኔ ምስክርና አቶ ኢዮኤል ነጋ ከሌሎች ተባባሪዎቻቸው ጋር በመሆን ላቋቋሙት መንፈሳዊ ድርጅቶች ያወጡትን የስራ ፈቃዳቸውን አብረን እንመልከት።

Saturday, April 10, 2010

የቤተክርስቲያናችን ችግሮች!!!

ውድ ምእመናን የቤተክርስቲያናችንን ችግሮች በተመለከተ ያቀረብናቸውን ጽሁፎች ስላነበባችሁ ክልብ እናመሰግናለን። ዛሬ ማህበረ ቅዱሳን ከቤተ ክህነት ጠቅላይ መምሪያ ተእዛዝና ተልኮ ውጭ በአምባ ገነንነት ወደ ምድረ አሜሪካ በመምጣት በሰበካ ቤተክርስቲያኖች ላይ ካደረሷቸው ጥቃቶች መሃል በሎስ አንጀሎሱ የኢትዮጵያ ተዋህዶ ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን ላይ ያደረሱትን ምእመናንን የመከፋፈልና የስም ማጥፋት ዘመቻ ይዘንላችሁ ቀርበናል። የእኛ ቤተክርስቲያን ላይ እያደረሱ ካለው ጥፋት ጋር ተመሳሳይ ሆኖ አግኝተነዋል።
አብረን እናንብበው። ምናልባት አስፈላጊ ትምህርት እናገኝበታለን ብለን እናምናለን።`

Thursday, April 1, 2010

የቤተክርስትያናችን ችግሮች!!!

ውድ አንባብያን ሆይ የቤተክርስትያናችንን ችግሮች በተመለከተ እስከዛሬ ድረስ ያቀረብነውን መረጃወች ስላነበባችሁ እናመሰግናለን። ዛሬ ደግሞ ማህበረ ቅዱሳን፦ 
1 በራሳችን ደብር ላይ ሲፈጽመው ከነበርው ዳባዎች መሃከል ጥቂቱን፦
2 ኢትዮጵያ ውስጥ የማህበሩ አባል አልሆንም ባሉ ካህን ላይ የድርጂቱ መሪ የሆኑት ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ያደረሰውን የስም ማጥፋት ዘመቻ ፍርድ ቤት ደርሶ የተሰጠውን የፍርድ ብያኔ፡-
3 ይህ ድርጅት ከሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ትእዛዝ ውጭ ሲያደርግ የነበረውን እንቅስቃሴ ለአብነት ያህል ይዘን ቀርበናል።
አብረን እናንብበው።-

Monday, March 29, 2010

የቢተክርስቲያናችን ችግሮች!!!
ውድ ምእመን ሆይ! ማህበረ ቅዱሳን በኦርቶዶክሳዊ እምነታችንና በወጣቱ ትውልድ ዙሪያ እያንዣበበ ለቤተክርስቲያናችን እድገት እንቅፋት ሆነው በመገኘታቸው በሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ በኩል ለቅዱስ ሲኖዶስና ለቅዱስ ፓትሪያርኩ የቀረበውን ጥናታዊ ጽሁፍ አብረን እናንብብ።

Tuesday, March 23, 2010

የቤተክርስቲያናችን ችግሮች!!

በተከታታይ የቤተክርስቲያናችንን ችግሮች በተመለከተ ወደፊት ተራ በተራ እናቀርብላችኋለን በማለት በገባነው ቃል መሰረት ዛሬ ደግሞ ማህበረ ቅዱሳን ቤተክርስቲያናችንን ከአንዳንድ እምነተ ደካማ ክሆኑ ተስፈኞች ጋር በመተባበር ያደረሰብን ጉድና ዘረፋ በኛ ላይ ብቻ የተፈጸመ ሳይሆን በሌላውም ላይ የደረሰ መሆኑንና ይህ ጋጠ ወጥነት መገታት እንዳለበት
“የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን መንበረ ፓትሪያርክ”
በማህበር ቅዱሳን ድርጅት ላይ የወሰነውን ዉሳኔ አብረን እናንብብ።