Monday, March 29, 2010

የቢተክርስቲያናችን ችግሮች!!!
ውድ ምእመን ሆይ! ማህበረ ቅዱሳን በኦርቶዶክሳዊ እምነታችንና በወጣቱ ትውልድ ዙሪያ እያንዣበበ ለቤተክርስቲያናችን እድገት እንቅፋት ሆነው በመገኘታቸው በሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ በኩል ለቅዱስ ሲኖዶስና ለቅዱስ ፓትሪያርኩ የቀረበውን ጥናታዊ ጽሁፍ አብረን እናንብብ።

Tuesday, March 23, 2010

የቤተክርስቲያናችን ችግሮች!!

በተከታታይ የቤተክርስቲያናችንን ችግሮች በተመለከተ ወደፊት ተራ በተራ እናቀርብላችኋለን በማለት በገባነው ቃል መሰረት ዛሬ ደግሞ ማህበረ ቅዱሳን ቤተክርስቲያናችንን ከአንዳንድ እምነተ ደካማ ክሆኑ ተስፈኞች ጋር በመተባበር ያደረሰብን ጉድና ዘረፋ በኛ ላይ ብቻ የተፈጸመ ሳይሆን በሌላውም ላይ የደረሰ መሆኑንና ይህ ጋጠ ወጥነት መገታት እንዳለበት
“የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን መንበረ ፓትሪያርክ”
በማህበር ቅዱሳን ድርጅት ላይ የወሰነውን ዉሳኔ አብረን እናንብብ።

Sunday, March 21, 2010

የቤተክርስትያናችን ችግሮች !!!!

ውድ ምእመን ሆይ!
ዶር. ግርማንና አቶ አበራን በገንዘብ ማጉደል ወንጀል ከሶ ምእመንን በቁጣ ስሜት ቀስቅሶ ከቦርድ ውስጥ ለማባረር የተደረገው ሙከራ መክሸፉ ይታወሳል። በተከሳሾች ላይ የቀረበውን ሰነድና ሁለቱ ተከሳሾች እንደ መረጃ ያቀረቡትን ሪፖርት እንድያጣራ የተሰየመው ቡድን ያደረገው ምርመራ የተጠበቀውን ተጨባጭ ውጤት ማምጣት አለመቻሉም ይፋ እየወጣ ነው። ቀድሞውንም ቢሆን በሃሰት የተቀነባበረ አድማ እንጅ የጎደለ ብር ስለሌለ ውጤት ያመጣል ተብሎ አልተጠበቀም ነበር። የኮሚቴው መመስረትና መቋቋም በእለቱ ሳያውቁትና ሳይጠብቁት ተከሳሾቹ ይዘው የቀረቡት ማስረጃ እፍረት ውስጥ ስለጣላቸው ድርጊታቸውን ህዝቡ እንዳይረዳና እንዳይሰማ ተከሳሾችም ማስረጃወቻቸውን ለህዝቡ በአግባቡ ሳያስረዱ ስብሰባዉን ለመበተን የተደረገ ሴራ ነበር። እንደተለመደው ያቀዱት አላማ ግቡን ካልመታ ህዝቡን ለማወናበድ ይችል ዘንድ ለዚህ ኮሚቴ አዲስ እቀድ ሰጥተውታል። ይህም አማራጭ ሃሳብ
1 የቀድሞ ቦርድ የተከፋፈለ ስለነበር አንድ ወጥ የሂሳብ ሪፖርት ይዞ መቅረብ አልቻለም!
2 አዲሱም ቦርድ ቢሆን እንደተለመደው የተከፋፈለ ስለሆነ ከቀድሞው ቦርድ የተሻለ ስራ ሊሰራ አይችልም!
3 በአዲሱ ቦርድ ውስጥ አደገኛ ሁኔታ የሚያመጡት ተከሳሾቹ ዶር. ግርማና አቶ አበራን ጨምሮ አዲስ የተመረጡት የቦርድ አባላት ናቸው፦
ብለው በሚጠሩት ስብሰባ ላይ ምእመኑን ለማሳመን እየተዘጋጁ ይገኛሉ። በጥቅም የተሳሰረ ቀለበት ውስጥ ያሉ ሰወች ከጀርባ ሆነው ቤተክርስቲያኑን ስለሚመሩ የህዝብ ድምጽ፤ መተዳደሪያ ደንብ፡ ለማስመሰል የተቀመጠ ሰነድ እንጅ ቤተክርስቲያኑ የኛ ነው የፈለግነውን ማድረግ እችላለን ብለው ያምናሉ። ስለዚህ ያለው ቦርድ እንዳለ ወርዶ በምትካቸው የምናውቃቸውን አዲስ ቦርድ አባላት መምረጥ አለብን ብለው አቅደዋል። ውድ ምእመናን ሆይ! በቀረበው መረጃ ላይ የተጠቀሱት ግለ ሰቦች ስም ዝርዝር የሚከተለው ነው።
1 ዲን. አለማየሁ ደስታ
2 ሻምበል ግዛው ገድሉ
3 አቶ አክሊሉ አፈወርቅ
4 አቶ መላኩ ታደሰ
5 አቶ ኪዳኔ አለማየሁ
6 ሟቹ የተከበሩ አቶ ሰይፈ ታደሰ
7 ወ/ሮ ንገሥት መኮነን
8 አቶ በትሩ ገብረእግዚአብሄር ናቸው።
መረጃው ላይ እንደምትመለከቱት ብሩን ከቤተክርስቲያን ለመውሰድ የፈጀባቸው ጊዚ ሶስት ቀን ብቻ ነበር። ቀደም ሲል በበጎ አድራጎት በኩል እርዳታ የጠየቃችሁ ምእመን ሁሉ እንደምታስታውሱት እድለኞች ሆናችሁ ከኮሚቴው እሽ የሚለውን የተስፋ ቃል ለመስማት ምን ያህል ጊዜ እንደሚፈጅባችሁ የምታውቁት ነገር ነው። ይህ ቡድን ግን ማመልከቻ ሳያስገባ በቃል ጥያቄ ብቻ ጉዳዩ ባጭር ጊዜ ውስጥ ሲፈጸምለት ይህው ሰነድ ያሳያችኋል። ጠይቁ ይሰጣችኋል እንደተባለው ከጠየቁት በላይ እጥፍ ብር ሲለገሳቸው መረጃው ያስረዳል። በመጨረሻም ቼኩ በማን ስም መጻፍ እንዳለበት አቶ መላኩ ታደሰ ተእዛዝ ሲሰጡና አቶ አክሊለ አፈወርቅም ባስቸኳይ ትእዛዙን ሲፈጽሙ እንመለከታለን። እርዳታ የጠየቀው ድርጅት ማንነት ግለጽ ሆኖ የሚመጣው እንደምታነቡት የፋክስ ትእዛዝ ከተላለፈ በኋላ ነው። በድረ ገጻቸው ላይ እንዳብራሩት በኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ስር የተደራጁ የኮሚቴው አንድ አካል ነን ብለዋል። እኛ እስከምናውቀው የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ በውስጡ የሬድዮ ዝግጅት ክፍልና በቅርቡ የተጀመረው መረዳጃ እድር እንዳሉት እናውቃለን። ይህ ራሱን አንድ ጊዜ “የኢትዮጵያ ዓይን ባንክ” ሌላ ጊዜ ደግሞ “ብሄራዊ የኢትዮጵያ ዓይን ባንክ” ዛሬ ደግሞ “ጊፍት ኦፍ ሳይት አላያንስ” በመባል የሚታውቀው ድርጅት የኮሚኒቲው ድርጅት መሆኑን አናውቅም። በየጊዜው ስሙን ለምን እንደሚለዋውጥ ግራ ገብቶናል። የህንን የሚያክል ግዙፍ ድርጅት ነኝ ባይ የራሱን ፍቃድ አውጥቶ ራሱን ችሎ ለመስራት ለምን አቃተው? ቀደም ብለን በጻፍነው ጽሁፍ ላይ የቤተክርስቲያኑ የሂሳብ ሰራተኛ የሆኑት አቶ ጌታቸው ሮቢና የቦርድ ተመራጭ የሆኑት ወ/ሮ ተዋበች ነጋሽ የሂሳብ ሰነድ ሲያሸሹ እንደተያዙ መጻፋችን ይታወቃል። በቀረበው መረጃ ላይ እንደምትመለከቱት እኝህ ው/ሮ ከላይ የተጠቀሰውን ድርጅት በሊቀ መንበርነት ሲመሩ የነበሩት የሟቹ የተከበሩ አቶ ሰይፈ ታደሰ ባለቤት ናቸው።እንዲሁም የተመረጡት የሂሳብ አገናዛቢ ቡድን አባላት የ2005- 2006-2007-2008-2009- ሰነዶች እየያዙ ውደቤታቸው እንደሚሄዱ መጻፋችን ትዝ እንደሚላችሁ ተስፋ እናደርጋለን። መረጃው ላይ የቀረበውም ሰነድ የ2005 ዓ.ም መሆኑን እንድገነዘቡ በዚህ አጋጣሚ አደራ አንላለን። እንዲያው ለነገሩ ለምርመራ የተረፈ ሰንድ አለ ብላችሁ ትገምታላችሁ ወይ?
መረጃው ላይ በዲያቆን አለማየሁ ደስታ በኩል የገንዘቡ ጥያቄ እንዲቀርብ ተጠቁሟል። እኝህ ግለሰብ የቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ ተብለው ተቀጥረው የቤተክርስቲያኑን ገንዘብ ለማህበረ ቅዱሳን ድርጅት ባገኙት አጋጣሚ ሁሉ እንደጅረት ውሃ ሲያፈሱ የነበሩ ሰው መሆናቸውን አትዘንጉ። ዛሬም በወ/ሮ ጥሩአየር ፍስሃ አማካኝነት ቤተ ክርስቲያንን እየከሰሱ ያሉ ግለሰብ ናቸው። ወ/ሮ ጥሩአየር ፍስሃ የአቶ ኪዳኔ ምስክር ባለቤት ሲሆኑ እቶ ኪዳኔ ምስክር የዲያቆን አለማየሁ ደስታ አጎት ናቸው። እንዲያው ለነገሩ አቶ መላኩ ታደሰና አቶ በትሩ ገብረእግዚአብሄር ከአቶ እዩኤል ነጋ ጋር በመሆን ቤተክርስቲያናችን አጠገብ ያለውን ህንጻ ለመግዛት የነበራቸው ህልም በምርጫው ውጤት መጨናገፉን ታውቃላችሁ ይሆን?
የዚህ የአይን ባንክ አምባሳደር የሆኑት አቶ ኪዳኔ አለማየሁ ”የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን አለም አቀፋዊ የምእመናን ማህበር” ሊቀ መንበር ናቸው። የቀድሞው ቦርድ ሊቀ መንበር የነበሩት አቶ ኢዮኤል ነጋ ደግሞ የማህበሩ ዋና ጸሃፊ ናቸው። ይህ ማህበር ከፓትሪያርክ ጳውሎስ ጋር በቅርበት የሚሰራ ድርጅት ነው። የዛሬ አራት አመትና ባለፈው አመት መጨረሻ ላይ የዚህ ድርጂት አመታዊ ስብሰባዎች እቤተክርስቲያናቸን ውስጥ ተስተናግደዋል። አቶ እዮኤልን በማስቀደም አባ ቆስጦስን የደብራችን ሃላፊ አድርገው በማስመጣት ቤተክርስቲያናችንን ለፓትሪያርክ ጳውሎስ ለማስረከብ ከፍተኛ ጥረት ያደረገ ድርጅት ነበር። ይህ ህልም ሲከሽፍ መላከ ሳህል አወቀ ተሰማን ያስቀጠረውም ይህ ቡድን ነው። በተጨማሪም አባ ቆስጦስን ጋብዘው መላከ ሳህል አወቀ ሲደልልን የደብራችን አለቃ አድርገው እንዲሾሙ ግፊት ሲያደርግ የነበረው ይህ ማህበር ነበር። ዲያቆን ዳንኤል ክብረትን በማስመጣት ማህበረ ቅዱሳን እንድንሰራራ ድጋፍ ለመስጠት ከፍተኛ ተጋድሎ ያደረገ ማህበር መሆኑ መዘንጋት የለበትም። ማህበር ቅዱሳን በቤተ ክርስቲያናችን ውስጥ የሚያደርጉትን እንቅስቃሴ የሚገታ ውሳኔ ለማሳለፍ በተደረገው ጥረት ላይ ይህ ድርጅት በወቅቱ በነበሩት የቦርድ ተመራጮች ላይ አሳድሮ የነበረው ተጽእኖ የከሸፈው በቅዱስ ሚካኤል ድጋፍ ነበር። ለዚህ እኩይ ሃሳብ አለመሳካት እንቅፋት ሆኑብን በማለት የቀድሞ የቦርድ አባላት ወ/ሮ ፈትለወርቅ ማማየንና አቶ ሃይሉ አራጋውን የተመረጡበትን የምርጫ ዘመን ሳይጨርሱ ከቦርድ ለማስወጣት በአቶ ኢዮኤል ነጋ በኩል የተደረገው ሙከራ የተቀነባበረው በዚህ ድርጅት በኩል ነበር። የቀድሞው ቦርድ ሊቀ መንበር የነበሩት አቶ ኢዮኤል ነጋ ማንንም ሳያማክሩ የፈለጉትን ሰው መቅጠር፡ ያልተጠበቀና እጀንዳ ያልተያዘለት ሃሳብ  ከየት መጣ ሳይባል እንኩ ፈጽሙ ብሎ ቦርድን አፍጦ ማስገደድ፡ በግል ኮንትራት መፈራረም፡ ከመተዳደርያው ደንብ ውጭ በማናለኝበት በመስራት፡ የተመረጡ የቦርድ አባላትን ለማስወጣት ለሁለተኛ ጊዜ ሲንቀሳቀሱ ይሄው እያያችሁት ነው። ቦርድ በስነ ስራት እንዳይሰራ አቶ እዮኤል ነጋን በማስቀደም ቤተክርስቲያኑን እያተራመሱ ካሉት ድርጅት መሃል በግንባር ቀደምትነት የሚጠቀሰው ይህ ድርጅት ነው።
ውድ ምእመን ሆይ!
የቤተ ክርስቲያናችንን ችግሮች ሰሞኑን ተራ በተራ እናቀርብላችኋለን፡ ብለን በገባነው ቃል መሰረት የጀመርነውን ዝግጅት በመቀጠል ሰሞኑን ከጠቅላይ ቤተ ክህነት ስለ ማህበረ ቅዱሳን የተላለፈውን መመሪያ እንድታነቡ እንጋብዛለን።

Thursday, March 18, 2010

የበተክርስቲያናችን ችግሮች!!!

በአቶ እዩኤል ነጋና በአቶ ጌታቸው ትርፌ የበላይ አቀነባባሪነት ሲመራ የነበረው አስተዳደር ቦርድ ለምርጫው ጥቆማ ከተደረገ ጊዜ ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ የሰሩትን ስራ በሙሉ ስላነበባችሁ እናመሰግናችኋለን። ዶር. ግርማንና አቶ አበራን ከቦርድ ዉስጥ ለማስወጣት ያዋቀሩት የሂሳብ አገናዛቢ ቡድንም ይህን ህልማቸውን እዉን ለማድረግ የተመረጠ ቡድን አንደሆነም ተገንዝባችኋል። ነገር ግን ይህ ቡድን ሁለቱን ግለሰቦች ብቻ ክቦርድ ማስወጣት አመርቂ ውጤት አያመጣም ብሎ አምኗል። በምርጫው አሸንፈው የገቡትን ጭምር ለማባረር ዝግጅት እያደረገ መሆኑን ደርሰንበታል። የተመረጠበት ደረሰኝ የማመሳከር ስራው እንደተጠበቀው ምንም ውጤት ስላላመጣለት አማራጭ አድርጎ የያዘው የቀድሞው ቦርድ ሆነ አሁን የተመረጠው ቦርድ ተነጋግሮ አብረው መስራት የማይችሉ ስለሆነ ሁሉም የቦርድ አባላት ከስልጣን ታግደው አዲስ ምርጫ ለማካሄድ ተስማምተዋል። የሚመረጡትም አድሶቹ የቦርድ አባላት ቀድሞ የነበረውን የምእመኑን ህብረትና ፍቅር መመለስ የሚችሉ ምርጥ የእኛ ወገን መሆን አለባቸው ብለዋል።
እነዚህ ግለሰቦች
1 የመተዳደርያ ደንቡን ቀድሞ ወደ ነበረው ህግ የሚመልሱ
2 የአባላት የወር መዋጮውን አንደቀድሞ የሚያደርጉ
3 ከሳሾችን ይቅር ብለው ደግሰው የሚቀበሉ ሰዎች መሆን አለባቸው ብለው ያምናሉ።
በዚህ መልክ የሚዋቀር የአስተዳደር ቦርድ አስፈላጊ የሆነበት ምክንያት ለምን ይሆን?
የቀድሞው ፍቅራችንና ህብረታችን የሚባለውስ ምንድነው?
ውድ አንባቢያን ሆይ! ይህንን ሴራ በደንብ ለመገንዘብ ትችሉ ዘንድ ቀደም ብለው ይሰሩት የነበረውን ስራ ሰሞኑን ተራ በተራ አናቀርብላችኋለን።
ለዛሬው እነዚህን መረጃዎች አብረን አናንብብ!
The Gift of Sight Alliance is a subsidiary of the Mutual Assistance Association for the  Ethiopian Community in Dallas/Fort Worth (MAAEC), a 501(c)(3) nonprofit organization. The Alliance was established to provide effective assistance to the Eye Bank of Ethiopia (EBE) which conducts surgery on blind people in Ethiopia enabling them to gain eye sight, some for the first time, years after their birth. The Alliance’s vision and objective is to eliminate preventable blindness in Ethiopia. The Alliance’s activities were initiated by Kidane Alemayehu, EBE’s Ambassador, as MAAEC’s Eye Bank support group chaired by the late Honourable Seyfe Tadesse, former President of the Ethiopian Parliament. With the active effort of the support group,
MAAEC was able to raise the required funds that enabled it to send a container load of medical equipment to Hawassa Hospital as well as to the Eye Bank of Ethiopia. Later, the support group expanded its base and renamed itself as the Gift of Sight Alliance with affiliated support groups in other US cities such as Seattle, Los Angeles, San Francisco, Detroit, Washington, DC, and Denver. Funds raised through these affiliates as well as supporters in Dallas/Fort Worth were received by the Eye Bank of Ethiopia. The affiliate in Seattle, headed by W/o Menkeli Kanaa, has been very active as it has managed to raise $10,000.00 first and later participated in the Alliance’s raffle sale all for the benefit of the EBE. W/o Menkeli deserves a special mention for her dedication and outstanding contribution for the production of a documentary film about the Eye Bank of Ethiopia and the establishment of this website.
The Gifts of Sight Alliance is currently chaired by Ato/Mr. Betru Gebregziabher. Header photo used under Creative Commons from babasteve  ·
Home
· About us
· How you can help
· Contact us

Tuesday, March 16, 2010

እውነትን በግልጽ እንዲያሳየን ለፈጣሪያችን ጸሎት እናደርስ!!


አቶ ጌታቸው የተባለው በሳምንት አንድ ቀን ላንድ ሰአት የቤተክርስቲያኑን ሂሳብ ለማዋቀር ገንዘብ የሚበላው ሂሳብ አዋቃሪ አቶ እዩኤል ነጋ አቶ ሃይሉ የድሮው ቦርድ ጸሃፊ አቶ አክሊለ ድሮ አስረኛ ክፍል ሳይጨርስ አዲስ አበባ አፍሪካ ማህበራዊ ድርጅት እርሳስና ወረቀት ለጸሃፊወች ለማደል የተቀጠረ ተላላኪ መቸም ስደት ለወሬ ይመቻልና ሂሳብ ክፍል ጸሃፊ ስለነበርኩ የሂሳብ አያያዝ አውቃለሁ የሚለውና አቶ መላኩ ጋር ሆነው ሁለቱን የቦርድ ተመራጮችን በሃሰት ከሰን አናባርራቸውና የድሮው ቦርድ እንደነበረ ይቀመጣል በማለት ክስ ሲጠነስሱ እባካችሁ ይቅርባችሁ ያላቸው ግለሰብ አንደሰማው ሁሉ በተለይም አቶ ጌታቸው ካልሆነልንና እዩኤል ክስልጣን ከወረደ ስራውን እለቃለሁ ብሎ በገባው ቃል ኪዳን መሰረት የስራ መልቀቂያ ደብዳቤ ሰሞኑን እንደሚያስገባ ይናገራሉ።
ከመልቀቁ በፊት ግን አዲሱ ቦርድ አዋቂ ሂሳብ ተቆጣጣሪ ተቀጥሮ ሂሳቡን ወደ ኋላ ተመልሶ ማጣራት አለበት በማለት ያቀረበው ፕላን ያስደነገጣቸው ከላይ የተጠቀሱት አብረው ቤተ ክርስቲያኑን ሲበዘብዙ የነበሩት አቶ አክሊሉና የቤተ ክርስቲያኑ ከሳሽ ባለቤት አቶ ኪዳኔ፡ አቶ ጌታቸውን ስራውን ለመልቀቅ ደብዳቤ ክማቅረቡ በፊት የድሮውን ሰነድ ሁሉ አንዲያጠፋ በተመከረው ምክር መሰረት ወይዘሮ ተዋበች የተባሉት የቦርዱ አባል ጋር ካርቶን ሞልተው የቤተክርስቲያኑን የሂሳብ ሰነድ እሮብ ቀን ከሰአት በኋላ ግቢው ጭር ባለበት ሰዓት ሊያሸሹ ሲሉ መያዛቸውን ሰምተን በጣም ተደናግጠናል።
አዲሱም ቦርድ ይሄን ሁሉ ነገር እያወቀ ሰነዱን እንዳለ ለማቆየት የውሰደው እርምጃ አስክዛሬ ድረስ ያለ አልመሰለንም። ሰነዱ ገንዘብ የተከፈለበት የቤተክርስቲያኑ ሃብት መሆኑ እየታውቀ ለምን ከቅጥር ግቢ ውጭ ለማውጣት ተሞከረ ብሎ የመረጥነው ቦርድ ያቀረበው ጥያቄና ቃል በገባውም መሰረት ለ ምእመን ያስታወቀው ነገር ስለሌለ መጥፎ ጥርጣሬ ዉስጥ አስገብቶናል። አቶ ጌታቸውም ወይዘሮ ተዋበችም በተለይም ይሂሳቡን ውዝግብ እንዲያጣሩ የተሰየሙት ኮሚቴውች ያልተባሉትን ሂሳብ ለማጣራት የ 2005፡ 2006 ፡ 2007፡ 2008፡2009 ሰነድ እንፈልጋለን እያሉ ሰነዱን ወደ ቤታቸው እየያዙ መሄዳቸውን ሰምተናል። እንደምታውቁት አጣሩ የተባሉት ከሳሹ አቶ ጌታቸው የቤተ ክርስቲያኑን ገንዘብ ባንክ ሳያስገቡ በሉት በማለት ያቀረበውን ሰነድና ተከሳሾቹ የለም አልበላንም በጊዜው ባንክ አስገብተናል መረጃውም ይሄው በማለት ያቀረቡትን የባንክ ሰነድ ማመሳከር እንጅ! በ 2006፣ 2007 ምን ያህል ገንዘብ ገባ ብላችሁ አጣሩ አልተባሉም ነበር። በ 2005 2006 2007 እነዚህ ተከሳሾች የቦርድ አባል እንዳልነበሩ እየታውቀ ለምን ይሆን እነ አቶ አክሊሉና አቶ ኪዳኔ ወይዘሮ አዜብ ጋር የድሮ ሰነድ የሚጠይቁት ብለን መጠየቅና ይኖርብናል።
በዚሁም አኳያ፡ አዲስ ኦዲተር ተቀጥሮ ወደኋላ ተመልሶ ለማጣራት የሚያደርገው ምርመራ በሚጀመርበት ወቅት ሰነዶች ሁሉ ተስተካክለው ባይቀርቡ ወይም ጠፋ ቢባል፦
1ኛ አሁን ያለው ቦርድ
2ኛ የ 2009 የሂሳብ መጉደልን እንዲያጣሩ የተመረጡትና የልተጠየቁበት ቦታ ገብተው መዝገብ ወደየቤታቸው እየያዙ የሚሄዱት የኮሚቴ ተመራጮች
3ኛ የቤተክርስቲያኑ ቅጥረኛ አቶ ጌታቸው
ተጠያቂወችና የወንጀል ስራ ተባባሪወች መሆናቸውን እንዲያውቁልን ለምእመኑ እናሳስባለን። 
ለአቶ ጌታቸውም በተለይ!
ለፍተን የምናገኘውንም የታክሲ ገቢ እንደዚሁ እያጭበረበረ እንዳያራቁተን አደራ እንለዋለን።
ሁለት ሰነድ ለማመሳከር ለተመረጡትም አጣሪ ኮሚቴ! አንዱን ሰነድ ከሌላው ጋር ለማመሳከር እንዴት ከሁለት ሰአት በላይ ሊውስድባችሁ ቻለ? እንኳን እናንተ ሂሳብ አያያዝ አዋቂወች ነን ባዮች ቀርቶ አኛ መሃይሞቹ በተከሳሾቹ በኩል የቀረበውን ሰነድ እዉነት ከባንክ የመጣ ሰነድ ነው ውይስ ልዩ?  ብሎ ማመሳከር  ከ አንድ ቀን በላይ አይውስድም።
ዋናው ተከሳሽ በፊርማ የተረከበውን ገንዘብ በጊዜው ባንክ አስገብቷል ወይ ?
ወይንስ ከሳሹ አቶ ጌታቸው እንዳቀረበው ማስረጃ አላስገባም!
ገንዘቡን በጌዜው አስገብቶ ከሆነ! ተከሳሹ የተውነጀለው በሃሰት ነው!
እንደቀረበውም ክስ መሰረት ካላስገባ! ባስቸኳይ እንዲያስገባ እንዲጠየቅ ለምእመኑ ሃሳብ ማቅረብ እንጅ እናንተው መርማሪ እናንተው ከሳሽ እናንተው ፈራጅ ሆናችሁ ለመቅረብ አስባችሁ ከሆነ ! ህዝቡ እንዲያውቅና ሽፍን አላማችሁን ብሎም የሂሳብ ሰነድ ማሸሻችሁን እንዲያጋልጥ በየ ተራ የምርምር ጥያቄውችን እንዲያቀርብ ለእውነት ቋሚ ሁሉ እናሳስባለን!!!!
በዚሁም አኳያ አት ኪዳኔ የከሳሽ ባለቤት ከመሆናቸውም በላይ የቤተ ክርስትያኑን ገቢ እስከ አስራ ዘጠኝ ሽህ ($19000) ፈርመው የተረከቡትን እስካሁን ስላልመለሱ በዚሁ ሳቢያ ምእመኑ ፊት ከመቅረባቸው በፊት እንዲመልሱ በትህትና እንጠይቃለን!!
ቶሎ ጊዜው ደርሶ እውነትን በግልጽ እንዲያሳየን ለፈጣሪያችን ጸሎት እናደርሳለን:
አሜን!!

Tuesday, March 9, 2010

ለዛሬ  ከhttp://selam-tewahdo.blogspot.com/ ከሚባለው ብሎግ "ጅራፍ እራሱ ገርፎ እራሱ ይጮሃል" በሚል ርእስ ከቀረበው ጽሁፍ አብዛኛውን ይዘንላችሁ ቀርበናል።

“ለ አይ አር ኤስ (IRS) በእጃችን ያለውን ማስረጃ አስረክበን ቤተክርስቲያኑን እናዘጋዋለን! መንግስት እንዲወርሰው እናደርጋለን! በኋላ ለምን እንዲህ አደረጋችሁ እንዳትሉን!” በሚል ርእስ ሰላም ተዋሂዶ በሚባለው የማህበረ ቅዱሳን ድረገጽ (ዌብሳይት) ተቀጥላ ብሎግ ላይ የተጻፈው የዘለፋና የማስፈራሪያ ጽሁፍ ሲሆን፤ እውነትም የሚካኤል ጠላቶች የገመዳቸው ጫፍ ላይ መድረሳቸውን ከጽሁፉ በግልጽ መረዳት ይቻላል።

የሚካኤልን ስእለት የበላ በሙሉ በያለበት እንዳበደች ውሻ እየተቅበዘበዘ ከመሆኑም ሌላ ወያኔው እና ለሆዳቸው የቆሙ ግብረአበሮቹ ከቦርድ አንወጣም ብለው ትንንቅ የፈጠሩትንና ሕዝብ አንቅሮ ተፍቶ ከቦርድ የመነቀራቸውን ይዞ፤ በየሰንበቴው ቤትና፤ በየስርቻው እየተሰበሰቡ ሲዶልቱ መክረማቸው ይታወሳል። “ይህን ሁሉ ያመጡብን ያ ዶክተርና አቶ አበራ ስለሆኑ አመጽ አስነስተን፤ ስማቸውን በክለን፤ ሕዝቡን አደናግረን ከቦርድ ማውረድ እና በምትካቸው ፈትለወርቅን መልሰን ማስገባት አለብን” ተብሎ የተሸረበው ሴራም ስለ ከሸፈባቸውና የዘረፉት የሕዝብ ገንዘብ ሲቆጠቁጣቸው አካኪ ዘራፍ!! እያሉ የሚቀበሩበትን ጉድጓድ ሲምሱ ይታያሉ።

Wednesday, March 3, 2010

ሰሚ ጆሮ ያለው ይስማ!!!!

የሚካኤልን ታቦት የከሰሱ ሰዎችን በማስቀደም ቤተክርስቲያኑን ለማፍረስ የሚታገሉት የወያኔ ተስፈኞች የጠሩት ስብሰባ መክሸፉን እንደሰማችሁ እናውቃለን። ህዝቡ እንደማይፈልጋቸው
፩ኛ፦ በምርጫ
፪ኛ፦ በጠሩት ስብሰባ ላይ ባለመገኘት እንደተፋቸው በድጋሚ አረጋግጦላቸዋል።

የሚካኤል ቤተክርስቲያን ከተቋቋመ ጀምሮ አንድ ጊዜ እንኳን በቦርድ አባልነት ተመርጠው  አገልግሎት ሰጥተው በማያውቁት በአቶ ጌታቸው ትርፌና ቤተክርስቲያኑ ከተመሰረተ ከቦርድ ወጥተው በማያውቁት በአቶ እዩኤል ነጋ አማካኝነት በቤተክርስቲያናችን ውስጥ የተሰገሰገውና የተሰባሰበው የፖለቲካ ድርጅት በቦርድ አባላት ምርጫ ላይ ተሳትፎ መሸነፉን ሁላችሁም የምታውቁት ነገር ነው።