Tuesday, September 29, 2009

እግዜኦ!!! አግዚኦ!!!
አቡነ ቆስጦስን ዎደኛ ቤት ክርስቲያን አስመጥቶ ቤት ክርስቲያኑን ለማስረከብ ሙከራ ሲደረግ
ሆዳቸው አልጨክን ያላቸዉ የቤት ክርስቲያኑ ዎዳጆች እንዳከሸፉት ብዙዎቻችን እናስታዉሳለን።
የዳላስ ቤተ ክርስቲያንም አልቀበላቸዉ ሲል በ ዋሽንግቶን ዲሲ አካባቢ ሆነው ያአባ ፓዉሎስን
ትዕዛዝ በስራ ላይ ሲያዉሉ መክረማቸዉ የታዎቀ ነው። በዚህ ዎቅት እኝሁን አቡን የተቀበሉት የ
ድ.ሲ ቤት ክርስቲያን መሪ ( በነገራችን ላይ ዶክቶሩ የ ሊቀ መንበራችን የገል ጓደኛ ) የዎያኔ
መንግስት ፕሬዚደንት ሊያደርጋቸዉ ነዉ የሚል ዎሬ በመላው አሜሪካ ያስነፍሱ የነበሩት ዶክተር
ናቸዉ።
እንዳጋጣሚ በዚሁ ዎቅት የደንቨር ቤት ክርስቲያን ደግሞ ካህን ይፈልግ ነበር። እኝህ በአሁኑ ጊዜ
እኛ ጋ የተጠጉትና መስቀልን እግዚአብሄር የተሰቀለበት ማስታዎሻ ከመሆኑ ይለቅ አንደ አንድ
የማንም የስራ መቀጠሪያ ድፕሎማ ገትረው ዲፕሎማየ ነው የትም ሄጀ መቀጠሪያየ ነው የሚሉት
ቄስ እንዲቀጠሩ ይጠቆማሉ ። ዪህ ጥያቄ አዲስ አበባ በደረሰ ጊዜ የለምንም ማጣሪያ ባስቸኩዋይ
ያባ ፓዉሎስን እቅድ ለሟሟላት እንዲመች ዎደ አሜሪካን ይላካሉ።
የመቅጠር ፍላጎት የነበረዉ ቤተ ክርስቲያን ሚስጥሩን ስለደረሰበት ሃሳቡን ለዉጦ ሌላ ቄስ
ሲቀጥር እኝሁ ጉደኛው የእኛ ቄስ ከአቡነ ቆፕስጦስ ጋር በ ዋሽንግቶን ዲሲ ቤት ክርስቲያን
ተዳብለው ሲበጠብጡ ኖሩ።
አቡነ ቆስጦስ የዳላስን ቤተ ክርስቲያን መረከብ ህልማቸዉ ስለከሸፈ መዕመናኑን ሊበትንና
ሊከፋፍል ይችላል ብለው ያመኑበትን እኝህን ቄስ ከዎያኔ መንግስት ተስፈኛ ፕሬዚዳንት ጋር
በመሆን በቤተ ክርስቲያናችን የቦርድ ሊቀመንበር አማካኝነት አስቀጠሩ።
የሄዉም ሊቀመንበራችን እኝህን ሰው ካስቀጠረ ዶክተሩ ፕሬዚዳንት ሲሆኑ አዲስ አበባ ሄዶ
የመንግስት ስራ ሊሰጠው ቃል እንደተገባለት ይህን ጉድ ያዎጣዉና ቤት ክርስቲያናችንን ከሽያጭ
ያዳነው ቡድን ገልጾታል።
እኝሁ ቄስ የተማመኑበትን ጋሻ ለማሳየት በየጊዝዉ በሚያሳዩት ተግባር እየገለጹ መሆኑ ለማንም
ድብቅ አይደለም።
ሁለት ጊዜ በተደረገዉ አጠቃላይ ጉባዔ ላይ ተነስተዉ መስቀላቸዉን ክፍ አድርገዉ ይዘዉ
እንጠቅሳለን (ይህን መስቀል እስከያዝኩ ድረስ የትም ሄጀ መስራት እችላለሁ) ብለዉ ደግመዉ
ደጋግመዉ ማስጠንቀቂያ ይሁን ዛቻ እንደነገሩን ሁላችንም ልብ ብለናል።
ይሄም የሚያሳየው የጨበጡት መስቀል ማዎናበጃ እንጅ እዉነት የክህነት ትምህርት አለመሆኑን
ነዉ። ዋና አላማቸዉ ህዝቡን ለመበታተን እንጅ እዉነትም የዕየሱስን ትምህርት ለማስተማር
እንዳልመጡ እየገለጹ መሆኑን ለዕናንተ ለመዕመናኑ እንድትረዱት ማድረግ አስፈላጊ
አይመስለንም የገዛ ስራቸዉ እየገለጠዉ ነዉ።
ፍትኅ ነገስት አንቀጽ 6 ቁጥር 210፦
ቄስ የእግዚአብሄር ሹም እንደመሆኑ ነዉር የሌለበት ይሆን ዘንድ ይገባዋልና፡ በራሱ ፍቃድ
የሚኖር አይሁን፡ ቂመኛ አብዝቶ የሚጠጣ ለመማታት እጁን የማያፈጥን አይሁን ያልታዘዘ
ትርፉን የሚዎድ አይሁን፡ እንግዳ መቀበልን የሚዎድ በጎ ስራን የሚዎድ ንጹህ ድንቀ ቸር የሆነ
ዎዘተ…
አንቀጽ 6 ቁጥር 224፦
የሃጢአተኛዉን ንስሃ የማይቀበል ዎይም በነገር ሠሪነት ሃሰትን በመመስከር የሚታበይ ሕግን
አዉቆ የማይሰራበት ክፉ ስራንም የሚያዘዎትር በጎ አለመስራትን የዎደደ ዎይም አለቃዉ
ሳይፈቅድለት ዎደ ንጉሥ የሚሄድ ቄስ ይሻር።
አንቀጽ 6 ቁጥር 234፦
በነገረ ሥራ አይመስክሩ ሰዉንም ለማክሰስ ዎደ ንⷝስ አይሂዱ፡ ሓሜተኞች አይሁኑ። ለመዕመናን
ክፋትን አይዉደዱ። ከነርሱ ዎገን ይህን ያደረገ ከሹመቱ ይሻር ዎዘተ…….
ቤተ ክርስቲያናችን ይህን መጽኅፍ የምትቀበል ከሆነ የእኛ ሁለቱ ቄሶች መቅደስ ዉስጥ ገብተዉ
መቀደስ ይችላሉ ዎይ?
ዎይስ የአስተዳደሩን ሥራዓት እንዳጣመምነው ዎደ መቅደሱም ችግሩን አስገብተን እያፌዝን
ነው።
ዋና ደጋፊአያቸዉ ያሁኑ ልቀ መምበር የመዕመናኑን መብት እየረገጠ የዎደፊት አገር ዉስጥ ገብቶ
ሊሾም መንገዱን እየጠረገ መሆኑን በግብር እያሳየ ነዉ።
ደግመን ደጋግመን ንስሃ እንዲገባ መለመናችንን አሁንም አንተዉም።
እሱ ግን ከቀን ዎደ ቀን በሚያሳየዉ ተግባር እየባሰበት መምጣቱንና አልፎ ተርፎ ከ ከሳሾቻችን
ገር በጥቅም እየተዋቀረ መሆኑን አጥብቀን መቆጣጠር ይኖርብናል።
በሚቀጥለዉ እትም ከከሳሾች ጋር የሚያደርገዉን ግኑኝነት እናበስራለን።

Friday, September 25, 2009

የሽማግሌን ኮሚቴ በአዲስ መልክ ለማዋቀር ጅምሩ ቀጥሏል!!!!!
የአስተዳደር ቦርድ የአማካሪ ኮሚቴ ብሎ ይጠራቸዋል፡ ህዝቡ ደግሞ የሽማግሌዎች ኮሚቴ ብሎ
ይላቸዋል። እንደት እንደተሰባሰቡ አልፈዉ ተርፈዉ ስማቸዉ ተሻሽሎ የቤተ ክርስቲያን ቋሚ
ኮሚቴ ለመሆን መብቃታቸዉን ሁላችሁም የምታዉቁት ታሪክ ነው።
ይህ በቋሚነት አገልግሎት መስጠት ላይ ያለው ኮሚቴ ክተቋቋመ ጊዜ ጀምሮ ያስገኘዉ ተጨባጭ
የስራ ዉጤት ምን ይሆን? የቤተ ክርስቲያናችንን ችግር ለመፍታት በተደረገዉ ጥረት ዚሁ
ኮሚቴ ድርሻ ምን ነበር?
ዎይስ ካሉን ችግሮች መሃል አንድ ዋናዉ ይሆን?
ለነዚህ ጥያቄዎችና እነማን እንደሆኑ እስከ ሽፍን አላማቸው ጋር ትንታኔ በዎቅቱ ዎደፊት
እናቀርባለን።
ለዛሬ ልንገልጽላችሁ የምንመኘዉ በማህበረ ቅዱሳንና በአባ ጳዉሎስ ተዎካዮች አማካኝነት
ተመርጦ በሽምግልና ስም ቤተ ክርስቲያናችን ዉስጥ መንቀሳቀስ ስለጀመረው ቡድን ይሆናል።
ይህ ቡድን ከአባ ፓዉሎስ ልዩ መልክተኛ ከ ንቡረእድ ጋር በማህበረ ቅዱሳን አማካኝነት
ተገናኝቶ በሽምግለና ስም እንዲቀሳቀስ ከተመረጠበት (August 18 2009) ዓ. ም ጀምሮ
እኛ እስከምናዉቀዉ ድረስ አራት ስብሰባዎች ሲያደርግ ሁለትን ያደረገዉ ከአስተደር ቦርዱ ጋር
ነው፡ ከላይ የተጠቀሱት ስብባዎች ሂደት እንደሚጠቁመዉ ዎደፊት ቋሚ የሽማግሌዎች ኮሚቴ
አባላት ለመሆን እየታጩ መሆኑን ይጠቁማል።
ከ ሰላሣ በላይ የሆን ማህበርተኞች የአስተዳደር ቦርዱን ለማነጋገር እንፈልጋለን ብለን በደብዳቤ
ብንጠይቅ ጥያቂአችንን ላለመቀበል የተለያየ ምክንያት በመፍጠር እንዲጓተት ተደርጓል፡
ሕዝቡን ቀርቦ ማነጋገር ያስፈራቸዉ ለምን የሆን?
ከላይ የተጠቀሰው የሽማግሌ ቡድን ግን የለፈው ቅዳሜ ማታ በስልክ ስብሰባ ጠይቀው ሰኞ ምሽት
ከቦርዱ ጋር መሰብሰባቸዉን እናዉቃለን።
በዚህ የአሰራር ልምድ ስለ ቦርዱ ለመገንዘብ የቻልነዉ ፦
የቤተ ክርስቲያኑ መዕመናን የመረጠዉ ቦርድ የተመረጠበትን አላማ ስቶ ለጥቅም ብቻ
እንደሚተዳደርና የመዕመናኑን ጉዳይ እና እሮሮ አልሰማም አሻፈረኝ እንደፈለጋቸዉ
ይሰደቡ!!ይሰዳደቡ!!! የት ይደርሳሉ?
የሚል አቋም እንዳለው ነው፡
የመረጠዉ መዕመናን ጋር ከሚገናኝ ይልቅ አባ ፓዉሎስ ከላኩት መለክተኛ ጋር መገናኘቱን
ለምን መረጠ ይሆን?
በኛ አስተሳሰብ ቦርዱ ከማህበረ ቅዱሳንና ካባ ፓዉሎስ በሚሰጠዉ መመሪያ እንደሚንቀሳቀስ ይፋ
ማዉጣቱን እያረጋገጠ መሁኑን ያስረዳናል።
እግዜር ቸር ዎሬ የምንሰማበትን ቀን ያቅርብለን።
በሚቀጥለው እትም ስለ ቀሳውስቱና በምን ዘዴ እንተቀጠሩልንና መስቀልን የጌታ እየሱስ ክርስቶስ
ምልክት መሆኑ ቀርቶ ማስፈራሪያ መደረጉን እንገልጽላችኋለን።

Wednesday, September 23, 2009

የእዉነት ያለህ
ቤተ ክርስቲያናችን ላይ የተሰነዘረው ጥቃት የተቀነባበረው በኢሃድግ መንግስት
ነው፡
በደካማ ጎናችን ገብቶ እያጠቃንም ነው፡ ይሕም ሊሆን የቻለው አስተዳደሩ ስራት
ያለምንም ማዕቀብና ቁጥጥር የተዋቀረ በመሆኑ ነው፡ በዚህም ምክንያት ከዉስጥና
ክዉጭ የተሞከረውን አደጋ መቋቋም አቅቶት ሲንገዳገድ ይታያል።
ባለፉት 19 አመታት የተከትልነው አስተዳደራዊ አስራር ተንዶ ለፍርድ ሸንጎ
ዳርጎናል።
ዎደፊት ለመጓዝና ይህን ብልሹ አስተዳደር ለመለዎጥ መፍትሄው፡ ግልጥ! ያለ
የአስዳደር (ትራንስፓረንሲ) ያለው አሰራር መዘርጋት ነው።
የህም ግልጥ አሰራር በሂሳብ መዝገብ አያያዛችን መጀመር አለበት የሚል ሃሳብና
ዕቅዱ ላስተዳደር ቦርዱ ቀረበ። ቦርዱ ግን ይህ የአሰራር ዘዴ ከቀረበለት ቀን ጀምሮ
ይህን እቅድ መቃዎሙን ተቀዳሚ ስራው አደረገ። ይባስ ብሎም ሃሳቡን ያቀረቡ
አባላትን ስም እየጠሩ ስራ አላሰራ አሉን በማለት የስም ማጥፋት ዘመቻን ስራየ
ብለው ተያያዙ። ለምን?
በ2007 ዓ.ም በበጎ አድራጎት ኮሚቲ አማካኝነት ዎጭ የሆነውንና እስከ ዛሪ ድረስ
ይህ ኮሚቲ ደረሰኝ ሊያቀርብበት ያልቻለውን ሰነዶች በ2008 ዓ.ም ላይ
ለመዕመናኑ መበተኑ ይታዎሳል። በዚህ ሰነድ ላይ ስማቸዉ የተዘረዘረው ግል ሰቦች
በሙሉ የዎሰዱትን ገንዘብ አባከኑት ተብሎ ክስ አልቀረበም? ይልቁንም የሰነዱ
መሰራጨት ዋና አላማ የነበረው ማህበረ ቅዱሳን በስሩ የሚተዳደሩ ቤተ
ክርስቲያናትና የራሱን የግል ስራ ለማስፈጸም በአንድ አመት ውስጥ ብቻ ስንት ብር
አንደዎሰደ ለማሳየት የተደረገ ሙከራ ነበር። ዓላማዉ በብዙ ዉጣ ዉረድ ግቡን
ሊመታ ችሏል፡ በዓንጻሩም የህ ሰነድ ዛሬ ይፋ ሆኖ ለመጣዉ ችግር ምክንያት
ሆኗል።
የአስተዳደር ቦርዱ በየሶስት ዓመቱ በሂሳብ አጣሪ (CPA) አስመርምሮ ለመዕመናኑ
የሚያሳዉቀዉን የሂሳብ ዝርዝር (ኦዲት) ማቅረብ ያቃተዉ በዚህ ለሕዝብ
በተበተንዉ ሰነድ ምክንያት ነው።
የኦዲተሩ አቀጣጠር ከመተዳደሪያ ደንቡ ዉጭ ያለምንም ጨረታ በትዉዉቅ መጥቶ
የተቀጠረ ሂሳብ ተቆጣጣሪ ነዉ። ይሄው ተቆጣጣሪ ቀደም ሲል ለቤተ ክርስቲያኑ
ተመሳሳይ አገልግሎት መስጠቱ አይዘነጋም። የሂሳብን መዝገቡ እንደምንፈልገው
በማቀነባበር አቅርብልን (COOK THE BOOK) ማለትም ዋሽልን ተብሎ ሴጠየቅ?
ሳያመነታ የደንበኞቹን ፍላጎት እንጅ የጠራ የሂሳብ የመቆጣጠር ስራ የሰራ
እይደለም።
ይኄዉ ግለስብ ባለፈዉ የአስተዳደር ቦርድ የዎጭ ሰነዶችን ደምረህ በምታገኘዉ
ቅምር ሂሳቡ እንደተዎራረደ አድርገህ አቅርብልን ብለው ቀጥረዉ እንደተጠየቀዉ
ሰርቶ በማቅረብ ኦዲት በ (C P A) ተደረገ ምንም የጎደለ ሂሳብ የለም ተብሎ
በጭብጨባ ሪፖርቱን መዕመናኑ እንዲቀበል ተደርጎ በሽፍንፍን መታለፉን
ሁላችንም እናውቃለን።
የዛሬዉም ቦርድ ይህንኑ አሰራር ለመድገም ቀና ደፋ ሲል ተደርሶበት፡ የለም ይህ
አሰራር ዖዲት ሳይሆን የዎጭ አጠቃላይ ድምር ዉጤት ነው ሲባል ልስራው
መጓተት ምክንያት ሆነ።
ዉድ መዕመናን አንድ ሰነድ ይህን ያህል የሰዉ ዓይን ክገለጸ ዎደ ኋላ የ አስር
ዓመት ሂሳብ ዖዲት ይደረግ ቢባል ዉጤቱ ምን የሚሆን ይመስላችኋል?
እኛ አባላቱ ይህን የመጠየቅ መብት የለንም ይሆን? ዎይስ ጥቅማቸዉ የተነካ
የዘራፊዎች ቡድን እንደሚያሰራጩት ዎሬ ይህን “ የፍሚጠይቁና የሚጽፉ የኛ
ሰዎች አይደሉም “ እየተባለ የኛ ሰዎች አይናቸዉን የከፈቱ አይደሉም
“ያደረግነውን ብናደርጋቸዉ የኛ የሆኑ አይቃዎሙንም” ገንዘባችንና አቅማችንን
አዋጥተን የጀመርነውን ቤት ክርስቲያን መበዝበዝ ቀርቶ መሸጥም እንችላለን እያሉ
ስለሚፎክሩ ከበይ ክፍል ያልሆነ ሁሉ የነሱ ሰዉ አይደለም ለማለት ይሆን?
እንድታዉቁልን የምንፈልገው እኛ አንዳዶቻችን ይሄ ዲርጊት በዛ ይቅር ሳያዋርደን
እናቁመዉና ዎደ መልካም ተግባር እንመለስ የምንል ነን ይሄንንም ያደረግነው
እናንተን ዘመዶቻችንና ጓደኞቻችን ትለቅ የሃፍረት ካባ እንዳትጎናጸፉ ነዉ።
በዚሁ ማስታዎሻ አማካይነት ግለጥ (ትራንስፓረንሲ) አሰራርን አብዛኛቹ የቦርድ
አስተዳደር አባላት የቀድሞዎቹም ሆኑ አሁን ያሉትና ደጋፊዎቻቸዉ ሽንጣቸዉን
ገትረው እየተቃዎሙ መሆናቸዉን እንድታዉቁ ለናንተ ለመዕመናኑ ማስረዳቱ ተገቢ
ነው፡ ይህም የሚሆንበት ምክንያት እንደ ድሮው እንደፈለግን እናደርጋለን እንጅ
ማንም እንዲቆጣጠረን አንፈልግም፡ አንዳንድ እነዙህ የኛን ሰዎች የሚነካ ጥያቄ
ሲነሳ አፍንጫ ሲነካ ዓይን ያለቅሳል እንደተባለው እኛዉ በኛዉ ተጠራርተን
እናፈርሰዋለን እንጅ ከ ዱሮው አሰራር አንዎጣም፡ ዘላለም እንደበዘበዝን አንኖራለን
እንደሚሉ ነዉ።
በሚቀጥለው እስትንገናኝ ደህና ሁኑልን።
ዎስብሃት ለዓምላክ።

Thursday, September 10, 2009

አልሞት ባይ ትጋዳይ።

የ ቦርድ አባሎቻችን በየቀኑ የምናስተላልፈዉን ጥያቄ በስራ ላይ ላለማዋል የሚያደርጉትን ጥረት በይፋ እያስታዎቁን መሆኑን ለናንተ ለምዕመናኑ ለንገልጽ እንፈልጋለን።
ጧትና ማታ ቤተ ክርስቲያናችንን አይናችን እያየ አብረው ካንዳንድ የቦርድ አባላት ጋር ሆነው የዘረፉንን እና በቤተክርስቲያናችን ዉስጥ እያሞለጩ የሚሰድቡንን (ፓራሳይት) አስዎግዱልን እያልናቸዉ እንዲያዉም ማን አለብን ብለው እነዚሁ ዘራፊዎች ዎር ተለዉጦ ሌላ ዎር ሲጀመር
የምንከፍተዉን የዎር መቁጠሪያ በገለጥን ቁጥር እያየን ሆዳችን እንዲቆስል፡ሊለጠፍ የሚገባዉ ስንት የቤት ክርስቲያን ምስል እያለ የማህበረ ቅዱሳንን የዘማሪ ምስል ለጥፈው ለመዕመናኑ መሸጣችዉን ልብ ብለን አይተናል።

ይሕንንም የቅሌት ስራ የፈጸመችው የቦርድ አባል ባስቸኩዋይ ህዝቡን ሰብስባ ይቅርታ በፍመጠየቅ የቸረቸረችዉን የቀን መቁጠሪያ ሰብስባ ሌላ ቤተ ክርስቲያኑን የሚዎክል የቀን መቁጠሪያ አሳትማ ለከፈሉት ሁሉ እንድታድል እንጠይቃለን።
ተሳዳቢ የዎያኔ ቄስ ከማስመጣትዋም በላይ ባለፈው ጊዜ እየተነገራት የማህበረ ቅዱሳን ዋና ተዎካይ የሆነ የስድስት ዎር ቄስ ቤተ ክርስቲያናችን ዉስጥ መጥቶ እንዲያስተምር አድርጋለች፡

በትላንትናዉም የቤተ ክርስቲያናችን ክስ ለከሳሾቻችን የተፈረደላቸዉን ፊርድ በሚመለከት የአባላት ስም ዝርዝር እንዲሰጥ ስለተደረገ መደሰቷን ደርሰንበታል።
ይህችም ዎይዘሮ ከበላይ ሆኖ የቦርድ አባላትን ዎደ ሸር መንገድ እንዲጓዙ የሚመራ ባለቤቷ ጋር
የጠነሰሱት መሆኑን በግለጽ ተረድተናል፡

ተጨባጭ የሆኑ ማስረጃዎችንም ከያዝነው ዎር አጋማሽ በኋላ በምናቀርባቸዉ አትሞችና የድምጽ ሲዲዎች እናቀርብላችኋለን፡
የሄ ሁሉ የቦርድ አባሎች ጥፋታቸዉን አዉቀው ንስሃ ክገቡ ማጋለጣችንን እናቆማለን ብለናል እስክዚያ ድረስ ግን አሁንም የቦርድ አባላት ሁሉ ዎደ መልካም ተግባር እንዲመለሱ እንጸልይላቸው!!!!!!።

Wednesday, September 9, 2009

መልካም ዎሬ ላንባቢዎቻችን፡
ቤተ ክርስቲያናችንን ከ (ፓራሳይት) እና ዉስጣችን ሆነው ሊሸጡን ከሚያስማሙን ከሃዲዎች ነጻ ለማድረግ የተያያዘው እሳት እየተቀጣጠለ ነው።
ዛሬ ደግሞ አዲስ ብሎግ “ ( ብሎግ) ምን ማለት እንደሆነ ለማያዉቁ መሃይማን ለዎደፊቱ እንተረጉምላችዋለን”
ማግኘታችንን ለናንተ ንጹህ ለሆናችሁ የ ቤተክርስቲያን አማኞች እናቀርባለን።
ብዙ ተከታታይም እንደሚኖረው ተረድተናል በጥሞና አንብቡት እንላለን
ብዙም ትምህርት እንደምናገኝበት አንጠራጠርም።


http://nenewe.blogspot.com/

በሰላም ቤተ ክርስቲያናችን አሸናፊ ይሆንልን ዘንድ መጸለያችንን አናቆምም፡

Sunday, September 6, 2009

ዛሬ ከብረዳሞ ብሎግ ላይ ያገኘነዉን ዎሬ ለናንተ የማህበረ ቅዱሳን ደጋፊዎች “ እነ አቶ ዒዩአል እና መላው የቦርድ አባላት” አፍኖ ይዞ ማህበረ ቅዱሳንና ከሳሾቻችን ቤተ ክርስቲያናችንን ይፈንጩበት እንደፈለጉም ያድርጓችሁ እንዲያዉም ብትዎዱም ባትዎዱም ልንታረቅና ዎደ ድሮው ልንመልሳችሁ ነው ብለው በሚስጥር ሳይሆን ባደባባይ ጠላቶቻችን ጋር እየዶለቱ መሆኑን እንድታዉቁልን ስለምንፈልግ ይሀኑ ብሎግ ኮፒ አድርገን እናትማለን፡
ፈቃድም እንደማያስፈልገን ተረድተናል።
ከዚህ እትም ጋር የምንስማማዉ ፍሬ ነገር ቢኖር፡ እኛም የተፈለገው ጥያቄ ተፈጽሞ ባስቸኳይ እስራላይ ከዋለ በያዝነው መንገድ ጉዞዋችንን እንደምናቆም ቃል እንገባለን።
የብሎጉ አድራሻ የሚከተለው ነው

http://debredamo.blogspot.com/
ዉድ የዳላስ ቅዱስ ሚካኤል ምእመናን፡
ባለፈዉ እትማችን ላይ አስተያየታችሁን ስጡን ብለን መጠየቃችንን እያስታዎስን
እንዳሰብነዉም ባይሆን ጥቂቶቻችሁ ያደረግነዉን አዳንድ የቀለም ስህተት እና የግል ጥላቻ
ያደረብን መሆኑን ገልጻችሗል።
ለማእመናኑ ለመግለጽ የምንፈልገው
አንደኛ፡
የኮምፒተርም ይሁን የመጻፍ ልምምድ የለንም፡ የቤተክርስቲያናችን ሁኔታ በጣም
ስላሳሰበንና መንገዱም ስላላማረን በተቻለን መጠን ዎደ መልካም መንገድ እንዲመለስልንና
እንደዱሮአችን ለጸሎት ስንገናኝ ተሳስመን ተሳስቀን አብረን በልተን ጠጥተን እስከሚመጣዉ
ጊዘ ጤና ይስጥለን ተባብለን እንድንለያይ ነዉ።
ከዛሬ አራት አመት ጀምሮ የሆነዉን ሁላችሁም ታዉቁታላችሁ። ቤታችንን ሰብሮ ገብቶ
ያበጣበጠንን በግለጽ ዓይናችን እያየ የዘረፈንን (ፓራሳይት) ለማባረር አስበን ነው።
ስለዚህ የቆሳቁስ ስህተቶቻችንን ታገሱና እለፉን።
ሁለተኛ፡
ከአቶ እዩኤልም ሆነ ከለሎቹ ጠብም ትዉዉቅም የለንም። አቶ እዩኤልን የምናዉቀው
እቤቱ ቁማር ስንጫዎት ማደራችንን እና የብዙዎቻችን ቤት ማፍረሱን ነው፡ ዋናዉ
ሃሳባችን፡ ማህበረ ቅዱሳን የተባለ የሰይጣን ተላላኪ ለነፍሱም ሆነ ለስጋዉ ልክ እንደ ቁማር
ማጫዎቱ የማይጠቅመዉ መሆኑን እንዲረዳ እና እነሱን ትቶ ዎደ መልካም ተግባር እንዲመለስልን
በማሰብ ነው።
(እንደምናውቀው የቅዱስ ሚካኤል ወፍጮ ጊዜዉን ጠብቆ ጠላቶቹንና የሚበዘብዙትን
እንድሚፈጭ አንጠራጠርም፡ ጊዜውንም ስለዎሰደ ያልፋቸዋል ማለት አለመሆኑን ይረዱ)
መመለሳቸዉንም የምናዉቀዉ ባስቸኩዋይ ቦርድ የቤተክርስቲያኑን አባላት ሰብስቦ ጥር ሰላሳ
አንድ ቀን ያሳለፉትን አዋጅ በስራ ላይ እንድዉል ሲደረግ ነዉ።
የፈሰሰ ዎሃ ተመልሶ እንደማይታፈሥ ስለምናዉቅ፡ የሂሳቡን የኦዲት ዉጤት ለኛ ማቅረብ በቦርዱ
ላይ የባሰ ሃሜትና መሳለቂያ መሆን እንጅ ምንም ፋይዳ እንደማያተርፍ አሁን ያለው ቦርድ
እንዲያዉቁት እንፈልጋለን።
ይህም ምክንያት ሆኖ ጊዜ የሚያራዝምበት ጉዳይ አይታየንም፡
እስክ እዚህ ዎር መሃከል ድረስ አንድ ዉጤት ካላገኘን ግን ትግላችንን እንደምንቀጥልና ይኽን
መልእክትና ሌሎችንም የተጨበጡ ማስረጃዎች እያቅረብን በእትም ብቻ ሳይሆን በድምጽ ማንበብ
ለማይዎደው ምእመናን እንደምንበትን እወቁለን።
ምእመኑን እንዲያዎናብዱ የምትልክዋቸው ግብረ አበሮቻችሁ ተሰብስበው ቤተክርስቲያናችን
ሊዎሰድ ነዉ ሊከሰስ ነው እያሉ ሃሰት የሆነ ዎሬ ማዉራታቸዉንም እናዉቃለን፡ ሁለት አይነት
ጸጉር ያበቀለ አዛዉንት እንዴት ያልሆነ ዎሬ ያዎራል እያልን እንደነቃለን።
አሁን ላላችሁት ቦርድ አባላት የምናሳስበው ባስቸክዋይ ኦዲት አስደርጉ ብሎ የመከራቹሁ እና ኦ
ዲተር ያቀረበላችሁ ግለሰብ ሊያዋርዳችሁ እንጅ ሊጠቅማችሁ እንዳልሆነ ተገንዘቡ ማንም
እንደሆነ ከነታሪኩ ከዚህ ዎር ግማሽ በኃላ በምናደርገው እትምና ድምጽ እናዎጣለን፣
ልዩ መልእክት፡ ላቶ እዩኤልና አሁን ላላችሁት የቦርድ አባላት.፤
እኛ ካንተ ጋርና ከሞላ ቦርድ አባላት ጋ ምንም ጠብ እንደሌለን አስቀድመህ እዎቅልን የኛ ዋናው
ጠባችን ከማህበረ ቅዱሳን ጋር አብረህ የምትዶልትበት ምክንያት ነው። ለምሳሌ ያህል ባለፈው
ዎር ከከሳሾቻችን ጋር በድብቅ ተገናኝተህ የተስማማኸዉን ስምምነት ተነግሮናል እንዲያዉም ማን
አለብኝ ብለህ ጨለማ ለብሰህ የቤተክርስቲያን በር ከፍተህ አስገብተህ ዉጭ በር ላይ ቆመህ
ጥበቃ ማድረግህን በአይናችን አይተናል.፡
እንዲሁም በይፋ የቤተክርስቲያን ከሳሾች የገንዘብ መሰብሰቢያ ወረቀት እያዞሩ ሲያድሉና
ሲያሳድሉ እያየህ ዝም ማለትህ የሚያሳፍር ተግባር ነው። ይህ ድርጊት አንተ ላይ ብቻ ሳይሆን
በመላው ቦርድ ላይ እንደሚያርፍ ቦርድ አባል የሆናችሁ ተረዱ።
በተጨማሪም ከዕግዚአብሄር ጋ የተላኩልን የቅዱስ ሚካዒል ቄስ እና የቦርዱ ዋና ጸሃፊ ባሉበት
አገር እያቁዋረጡ የሚመጡት የዎያኔና ያባ ፓዉሎስ ተዎካይ በግለጽ ድቪድ እና ጥብቆ ሲሸጡ
ዝም ብለው ሲያዩ እንደነበረ ሰምተናል፡
ይህም ዋና ጸሃፊ አስቆምኩዋቸው ማለቱን ሰምተናል፣ሸጠው ሲጨርሱ ማስቆምና ዎዲያው እንዳየ
ፖሊስ ጠርቶ ማስነጠቅ ተግባሩ እንደነበረ የዘነጋው ይመስላል፡
ምዕመናን ሆይ እኛንና እንደናንተ ያለዉን የ ማህበረ ቅዱሳን ደጋፊ ያልሆነዉን ይሀዉ ጸሃፊ ይሄን
ስራ ሰንሰራ ቢያይ እንደሚያሳስረን አትጠራጠሩ፤
አንዱ የቦርድ አባል የሚያደርገው ሃጤአት ሁላችሁንም የቦርድ አባላት እንደሚያስዎቅስ
እንድታዉቁለን እንፈልጋለን።
እባካችሁ ለኛም ለነብሳችሁም፤ ማህበረ ቅዱሳን ሳይሆን በብዛት ለመረጣችሁ መምእመናን ስትሉ
የተመረጣችሁበትን ዋና አላማ አድርጋችሁ እኛ ምእመናኑ ደስ ብሎን ቅዳሴ ልቡን
ለእግዚአብሔር የሰጠ ቄስ (ባለፈው ስብሰባላይ ላይ ከልብ የሆነ ምስጋና በቅን ልቦናችሁ
ያፈሰሳችሁለት) አይነት ቄስ ፈልጋችሁ አምጡለን እንላለን።
በግልጽ ማህበረ ቅዱሳን መሆኑን አያሳየ በስድስት ዎር የቅስና ሹመት የተሰጠዉና መቅደስ ዉስጥ
ገብቶ የሚያበጣብጠዉን ቄስና ደጋፊዉን ዘባራቂ የእግዚአብሄር መልዕክተኛ አዎናባጅ
አስዎግዱልን እንላለን።
የጠየቅነው ጥያቄ እንዲፈጸምለን ለዓምላክ ከፍተኛ ጸሎት እናቀርባለን!!! ጸሎታችንንም
እንደሚሰማን አንጠራጠርም።
እስከተፈጸመልንም ድረስ በሰላም እንሰናበታችሁዋለን።
መልካም በአል ያድርግልን።
ደህና ሰንብቱ ብለን እዚህ ላይ እንዘጋለን።

Saturday, September 5, 2009

በቅርቡ አዲስ የምናዎጣውን ዜና እስትናቀርብ ድረስ ለናንተ ለቤተ ክርስቲያችን ተቆርቁዋሪዎች
የተከተለዉን የሃገር ፊቅር ራድዎ እንድታዳምጡ እንጋብዛለን፤
ይህ ሬድዮ ጣቢያ በኛ ቤተ ክርስቲያን ላይ የደረሰዉንና እየደረሰም የሚ
ገኘዉን የማሕበረ ቅዱሳን ተግባርና ግብ በግልጽ ያሳያል፤ በተለይም
የመጨረሻው ቁጥር 823 እና 830 ያዳምጡ፡
ላልሰማዉም ሁሉ ያዳርሱ እንላለን።


http://www.wmet1160.com/?page_id=136