Wednesday, December 23, 2009

የክርስትና ኃይማኖት ተከታዮች ነን? እስቲ እራሳችንን እንመርምር!!

ለእውነት ታማኝ መሆንህንና እውነትን ይዘህ መኖርህን ሲመሰክሩ በመስማቴ በጣም ደስ አለኝ። ምክንያቱም ልጆቼ እዉነትን ይዘው መኖራቸውን ከመስማት ይልቅ ሌላ ይበልጥ የሚያስደስተኝ ነገር የለም።
3ተኛው የዮኅንስ መለክት ቁጥር 3:4

እነሱ የወጡት ከኛ መካከል ነው። ይሁን እንጅ ድሮውንም ከኛ ወገን አልነበሩም። ከኛ ወገን ቢሆኑማ ኖሮ ከኛ ጋር ጸንተው በኖሩ ነበር። ነገር ግን ሁሉ ከኛ ወገን አለመሆናቸው እንዲታወቅ ከኛ መካከል ተለይተው ወጥተዋል።
1ኛ የዮሃንስ መለክት 2:19

እነዚህ ሰዎች በህልም እየተመሩ ስጋቸዉን ያረክሳሉ፡ የእግዚአብሄርንም ስልጣን ይንቃሉ። በሰማይ ክብር ያላቸውንም ይነቅፋሉ። የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል እንኳ ስለ ሙሴ አስከሬን ከዲያብሎስ ጋር በብርቱ በተከራከረ ጊዜ “እግዚአብሄር ይገስጽህ” አለው እንጅ የስድብ ቃል በመናገር ሊፈርድበት አልደፈረም።
የይሁዳ መለክት ቁጥር 8

የክፉ ሰው ሃጢያት እንደ ወጥመድ ነው። ስለዚህ የገዛ ሃጢያቱ ወጥመድ ሆኖ ይይዘዋል።
ምሳሌ 5:22

እግዚአብሄር የሚጠላቸው ስድስት ነገሮች አሉ። እንዲያውም እርሱ የሚጸየፋቸው ሰባት ናቸው።እነሱም፦ በንቀት የሚመለከት ዓይን፤ ሃሰት የሚናገር ምላስ፤ ንጹሆች ሰዎችን የሚገድሉ እጆች፤ ክፉ ሃሳብ የሚያፈልቅ አዕምሮ፤ ወደ ክፋት ለመሮጥ የሚቸኩሉ እግሮች፤ በውሸት ላይ ውሸት እየጨመረ የሚናገር ምስክር፤ በወዳጆች መካከል ጠብ የሚያነሳሳ ሰው ናቸው።
ምሳሌ 6:16-19

አስተዋይ መሆን ያስከብራል። ከዳተኛነት ግን ወደ ጥፋት ያደርሳል። አስተዋይ ሰዎች ለሚሰሩት ስራ አስቀድመው እቅድ ያወጣሉ። ማስተዋል የጎደላቸዉ ስዎች ግን አላዋቂነታቸዉን ይገልጣሉ። የማይታመኑ መለክተኞች ሁከትን ይፈጥራሉ። ታማኞች ግን ሰላምን ያስገኛሉ።
ምሳሌ 13:15-17

የሃሰት እድሜ አጭር ነው። እውነት ግን ለዘላለም ትኖራለች።
ምሳሌ 12:19

ወዳጄ ሆይ! ደጉን ምሰል እንጂ ክፉውን አትምሰል። ደግ ስራ የሚሰራ ሁሉ የእግዚአብሔር ነው። ክፉ ስራ የሚሰራ ግን እግዚአብሔርን አላየውም።
3ተኛ የዮሓንስ መለክት ቁጥር 11

Tuesday, December 22, 2009

መልካም ዜና ለጌታችን ልደት !!!!!
ወዳጆቻችን በሙሉ እንኳን ደስ አለን !!
በኢትዮጵያ መንግስትና በማህበረ እርኩሳን መእመናኑን ለመከፋፈልና እርስበርሳችን ለማጋጨት
ሰንዝረዉት የነበረው ክስ እንደገና ለሁለተኛ ጊዜ ከሸፈ።
ቅዱስ ሚካኤልን የሚዘርፉት ገንዘብ ሲታገድባቸው በንዴት ወደ ክስ የሄዱት ማህበረ ቅዱሳንና
ግብረ አበሮቻቸው የመሰረቱት ክስ ሁሉ በሙሉ በቅዱስ ሚካኤል ረዳትነት ካሽፏል።

Tuesday, November 10, 2009

አስቸኳይ ጥሪ !!!!
በጠቅላይ ሚኒስተር መለሰ ዜናዊ አማቾች የበላይ አቀነባባሪነት የሚንቀሳቀሰው የአስተዳደር ቦርድ
November 6 2009 ዓ.ም ከቤተ ክርስቲያኑ ጠበቃ Mr. Lloyed Ward የተላከለትን ደብዳቤ
አፍኖ ይዟል። ደብዳብፌው ከሳሾች ቤተ ክርስቲያኑን ላባ ፓዉሎስ አሳልፎ ለመስጠት ካልሆነም
ለማፍረስ ቆርጠዉ የተነሱ ስለሆነ ዛሬ ይህን አላማቸዉን ከግብ ለማድረስ ተጨማሪ የክስ ሰነዶች
አባሪ በማድረግ ቀጠሮ ለ November 11 2009 ዓ.ም መያዛቸዉን ያስረዳል።
ፍርድ ቤቱ የቀረበለትን የክስ ሰነድ ካመነበትና ከተቀበለዉ ክሱ ብያኔ እስከሚያገኝ ድረስ
1 ቤተ ክርስቲያኑ በዉጭ ሰዎች ሞግዚትነት ይተዳደራል፡
2 አሁን ያለዉ ቦርድ በሙሉ ከስራ ይታገዳል፡
3 ምርጫ አይደረግም፡
4 አዲሱ ህግ ተሽሮ በድሮዉ ህግ እንተዳደራለን፡
5 ቤተ ክርስቲአያን የሚመጣ ስዉ ሁሉ አንደ አባል ትቆጥሮ የድምጽ መስጠት መብት
ይሰጠዋል።
እነዚህ ክብዙ በጥቂቱ የቀረቡ ተጨማሪ ክሶች ናቸዉ።
በኛ ግምት ከነዚህ ከሳሾች በስተጀርባ ከፍተኛ ሃይል እንዳለ አንጠራጠርም።
ካባ ፓዉሎስና ከጠቅላይ ሚኒስተሩ ጽህፈት ቤት በሚላክ ገንዘብና ድጋፍ እንደሚንቀሳቀሱ
ተደርሶበታል።
ስለዚህ November 11 2009 ዓ.ም ከጡዋቱ ዘጠኝ ሰአት ላይ 600 Commerce St
192nd District court
George L Allen Sr. Court Bldg.
Dallas Tx 75202
በመገኘት ድጋፋችንን ለቤተ ክርስቲያናችን ማሳየት ተገቢ ነዉ።
ህዝቡን በዚህ መልክ ከማስተባበር ይልቅ የጠቅላይ ሚኒስተሩ አማች የመስተ እንግዶ ኮሚቴ
ሰብሳቢ ከቦርዱ ሊቀ መንበር ጋር በመሆን ባለቤታቸዉን እና ታዛዣአቸዉ የሆነዉን ዋና ጸሃፊ
ደግሞ ለማስመረጥ በመሯሯጥ ላይ ናቸዉ።
ከስድስት ዎር በላይ መዋጮ ያልከፈለ ለመመረጥም ሆነ ለማስመረጥ እንደማይችል እያወቁ
የልጠረጠሩ ጓደኞቻቸዉን በተለመደዉ የቅጥፈት ባህሪአቸዉ ዋሽተዉ መመረጥም መምረጥም
እንዳሚችሉ ቃል እየገቡ ገንዘብ በጸሃፊዉና በኦዲተሯ አማካኝነት እየሰበሰቡ ይገኛሉ።
የህ ሁሉ መእመን እዉነቱን ካወቀ የቤተ ክርስቲያኑን ህግ ለመስበርም ሆነ ለከሳሾች መረጃ ሆኖ
ለመቅረብ እንደማይተባበራቸዉ እናምናለን።

Wednesday, November 4, 2009

ውድ የቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን አባላት ሆይ!!
አበው ሲተርቱ “ሲሾም ያልበላ ሲሻር ይቆጨዋል” እንዲሉ፤ እነ የቦርድ አባላት
የሚዘርፉት ሳያንስ በየአገልግሎት ኮሚቴው የተመረጡት ሁሉ የሹመት ምልክት መበዝበዝ ነው፤
ካልሆነም እንደስልጣን መጠቀም ነው፤ እያሉ በቦርዱና በየኮሚቴዎቹ ተሰግስገው
ቤተክርስቲያናችንን ሲያራቁቱ ምእመናኑን ሲያደሙ መቆየታቸው ከኛ አልፎ በአለም ዙሪያ ባሉ
አብያተክርስቲያናት እና ኢትዮጵያውያን ሲነገር መስማቱ የሚያሳፍርና የሚያሳዝን ነው። ጌታችንና
መድሀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በቤተመቅደስ ሲሸጡና ሲለውጡ እንዲሁም ብዙ ጸያፍ
አድራጎትን ሲፈጽሙ ስላገኛቸው ሃሳውያን ሲናገር “ቤቴ የጸሎት ቤት ይባላል፤ እናንተ ግን
የሌቦች ዋሻ፤ የቀማኞች መሸሻ አደረጋችሁት” ብሏል (የማቴዎስ ወንጌል ፳፩፡፲፪)። እኛም እዚሁ
ቁጭ ብለን እኒሁ በዝባዦች “ቤተክርስቲያኗን የመሰረትናት እኛ ነን፤ ሌላው ሰው ምን አባቱ
አገባው፤ እንኳን መዝረፍ ምንስ ብናደርግ” በማለት ሲመጻደቁ እየሰማን፤ የሚያደርጉትን
አያውቁምና ይቅር በላቸው! ስንል ቆይተናል። በጥቂቱ ለመጥቀስ፦ የስለት፤ የሙዳየ
ምጽዋት፤የበጎ አድራት፤ የእደሳ፤ የጥገና፤ የእቃ ግዥን ጨምሮ ሲዘረፍ የኖረውን መጥቀስ
ይበቃል። አሁን ግን የተሾሙት የሚወርዱበት የዘረፉት ወደሕግ ፊት የሚቀርቡበት ቀን
እየተቃረበ ስለመጣ፤ የዚህ አይነት ጸያፍ ባህል ተካፋይ አንሆንም በማለትና በተለያየ ምክንያት
ከቤተክርስቲያን የራቃችሁ ሁሉ እንድትመለሱና እግዚአብሔርን በምትችሉት መንገድ ሁሉ
እንድታገለግሉ ከፍተኛ ጥሪ እናቀርብላችኋለን። የፈለጉትን ያድርጉ እኔ ምን አጨቃጨቀኝ
የሚባልበት ዘመን አልፎ፤ የእግዚአብሔርን ለእግዚአብሔር የቄሳርን ለቄሳር ስጡ የሚለውን
መመሪያ በተግባር የምናውልበት ዘመን መጥቷል።
የአስተናጋጅ ኮሚቴ ዋና ሆነው የተመረጡትም በነአለማየሁ አስተዳዳሪነት ወቅት በማህበረ
ቅዱሳን ሙዳየ ምጽዋት ሰብሳቢነት ጊዜ ይችን ለናንተ ይችን ለኛ እየተባባሉ ሲበዘብዙ
መኖራቸው ለናንተ ለምታውቋቸው ስውር ነገር አይደለም።
በጣም የሚያስገርመው ደግሞ ያ ሁሉ ካለፈ በኋላ አሁንም ወደበፊቱ አሰራር
እንድንመለስ ባለቤታቸውን እና ግብርአበራቸውን በቤተክርስቲያን ውስጥ በሃሰት ለመመስከር
ይሉኝታ የሌለውን ጸሃፊ በድጋሜ ለማስመረጥ እየተሯሯጡና በየቦታው ጓደኞቻቸውን እየተማጠኑ
መሆናቸውን ሰምተናል።
አልፎ ተርፎም ምክትላቸውን አስመራጭ ኮሚቴ አስገብተዉ ይሄ የማይገኝ ስልጣን
ስለሆነ ተጠቀምበት ብለዉ ስላዘዙት እሱም በበኩሉ በየቀሳውስቱ ሳይቀር እባክዎ አማልዱኝ፤ ዋና
ጸሃፊዉና የአለቃየ ባለቤት እንድትመረጥ እርዱኝ እያለ መማጠኑን ደርሰንበታል። ይህ ግለሰብ
አስመራጭ ኮሚቴ መግባቱ ህዝብን በቅን መንፈስ እንዲያገለግል እንጅ ለመጠቀሚያ
አለመመረጡን ያስተማረው ስለሌለ አስመራጭ ኮሚቴ ገብቶ እከሌንና እከሌን ብቻ ምረጡ እያለ
ሊበጠብጥ ነው ማለት ነው።
ካሁን ቀደም እንደገለጽነው ለአስተዳደር ቦርድ አንድ ግለሰብ ሲመረጥ ኑሮውንና ጉልበቱን ለኔ
ሳይል በበጎ ፈቃድ ለእግዚአብሄር እንዲሰጥ ሲጠየቅ ብዙወች ቶሎ እሽ ስለማይሉ እየተለመኑና
እየተማጠኑ ነበር የሚመረጡት።
እዚህ ቤተክርስቲያን ግን ለቦርድ አገልግሎት መመረጥ እንደ አገራችን ሹመት ስለሚመስላቸው
ከምረጡኝና አስመርጡኝ አልፎ እከሌና እከሌን መምረጥ አለባችሁ የሚባል በሽታ መጥቷል።
ከተመረጡ በኋላም ጊዜአቸውን ሲጨርሱ አንወርድም የሚሉም አልታጡም። ይሉኝታም
ኃፍረትም ቀርቷል፤ ዘረፋው በይፋ ቀጥሏል። የሌባ አይነደረቅ መልሶ ልብ ያደርቅ እንደሚባለው
ያለደረሰኝ የሚሰበሰበው ገንዘብ የት እይገባ እንደሆነና አላማውም ምን እንደሆነ በሚቀጥለው
እትም እንገልጻልችኋለን። በቸር ይግጠመን!!

Friday, October 30, 2009

እርምጃ መዉሰድ አስፈላጊና ማብታችን ነዉ!!!
እንድታዉቁት ያህል!
ካሁን ቀደም የቦርዱ ሊቀ መንበራችን ቤተ ክርስቲያናችንን ላባ ፓዉሎስ ሊሸጥ ተስማምቶ አቡነ
ቆስጦስን ለማስመጣትና ለማስረከብ ተደርሶበት እንዳልተሳካለት ስንነግራችሁ ልታምኑን
ያልቻላችሁ ሁሉ ለነ አቶ አፈ ቀላጤወች ትልቁ ማስተማኛ ይሄዉላችሁ።
ይሄዉ ሊቀ መንበር ጥር ስላሳ አንድ ላይ ያወጀዉን የቦርድ አዋጅ በመጀመሪያ ቤተ
ክርስቲያናችን ገለልተኛ ነች በተከታይ 501 c ያላቸዉ ቡድንም ሆነ ማንኛዉም ማህበር የቤተ
ክርስቲያኑ መምበር አይሆንም እያለ ይሄዉላችሁ እራሱ ህጉን እየጣሰና እራሱን ብቻ ሳይሆን
የቦርድ ግብረ አበሮቹንና የግል ጓደኞቹን እነ ዶክቶር…. እነ አቶ… እያዋረደ ነዉ።
(ስልካቸዉን ላባ ፓውሎስ በጻፈው ደብዳቢ ላይ ይገኛል)
በጣም የሚገርመዉ እኝህ ዶችቶር ጓደኛዉ አለም አቀፍ ድርጂት ሲሰሩ ኖረው አርፈው ያለ
ምንም ጭቅጭቅ ጡረታቸዉን እግዚአብሄርን እያመሰገኑ በመኖር ፋንታ እዚህ ቁማርተኛ ነጋዴ
እኩያቸዉ ያልሆነ ሰዉ ጋር ዶልተው የሰዉ ስም ሲያጠፉ እየታዩና ቤተ ክርስቲያን ለመሸጥ
እያስማሙ መሆናቸዉን ለአባ ፓዉሎስና ለአዲስ አበባዉ ሲኖድ እንጠቅሳለን “እኛ በዓለሙሁሉ
ተሰራጭተን የምንገኝ ተባባሪዎች” በማለት መማጠናቸዉን እራሳችሁ አንብቡ።
በተደጋጋሚም ልንገልጽላችሁ የምንፈልገዉ አቶ ሊቀ መንበርና እነዚሁ ጓደኞቹ የቴክሳስ ቀረጥ
ነጻ ግብር ክፍያ 501 c አዉጥተዉ ገንዘብ እየሰበሰቡ መሆናቸዉን ላላወቃችሁ ሁሉ እውቁ
እንላለን።
እኝሁ ዶክቶር ጓደኛዉ ባለፈዉ ጥቂት ስብሰባ ላይ ይሄዉ ሰነድ ሲነበብ ሊቀ መንበሩ እኮ የጻፈው
በግሉ ነዉ በማለት ሃፍረታቸዉን ተጎናጽፈዉ ሄደዋል።
አፈ ቀላጤዉም ይሄ ድርጊት አዋራጅ መሆኑን ተመልክቶ አቶ ሊቀ መንበር ይሄን አይጽፍም
እያለ በሃይል ቃል ሲያስተባብል መዋሉን ልንገልጽላችሁ እንወዳለን። ይህንኑ ግለ ሰብ ጓደኛችንን
የዎያኔው ተጠሪ በዳላስ ከተማ ያሉት የቤተ ክርስቲያኑ አስተናጋጅ ኮሚቴ ዋና ሹምና የሊቀ
መንበሩ ብቻ ሳይሆን የማህበረ ቅዱሳን ደጋፊ ዉስጠ ሚስጥሩን ሳይነግሩት በየ ስብሰባዉ ላይ ሁሉ
እንዲጋፈጥ አድርገዉታል።
እጥብቀን ይህን ጓደኛችንን የምንመክረዉ ለነሱ ስትል ስምህን አታጥፋ ነው።
በተጨማሪ ልናሳስባችሁ የምንፈልገው የቦርዱ ጸሃፊ ህዝብ በተሰበሰበበት የመዕማናን ስብሰባ ላይ
ለዛሬ ሳይሉ ግጥም አድርገዉ መዋሸታቸዉን ነዉ እንጠቅሳለን “ የቤተ ክርስቲያኑ ከሳሾች
እቤተ ክርስቲያኑ ዉስጥ ያስገበኋቸው እኔ ነኝ እንጅ አቶ ኢዩኤል እይደለም፡ እንዲያዉም
በቦታው አልነበረም” ብሎ በአይናችን ያየነውን ለማስተባበል ሞክሯል።
ይሄ ሃሰተኛ የቦርድ አባል መሆን ይገባዋልን?
እናንተው ፍረዱ።
በድጋሜም ለቦርድ የምርጫ ኮሚቴ ድሮ የተሰናበተው የማህበረ ቅዱሳን የትምህርት ኮሚቴ
አሁንም ስላለ የምርጫ ኮሚቴ ዉስጥ መግባት አለበት እያለ ማወናበዱን ሰምተናል።
ዉድ ማህበርተኛ ሆይ፦
እነዚህን የቦርድ ሊቀ መምበርና ይህን ከሃዲ ጸሃፊ ምርጫዉ ከመካሄዱ በፊት ማባረር ይገባናል
ብለን ስለምናምን ሰሞኑን ስብሰባ ጠርተን እንዲዎርዱ እንጠይቅ።
በትናንትናው ቀን በሽምግልና ስም አይን ያወጣ ድርቅና!!!! ብለን መጻፋችን ይታወሳል!
ቦርዱ ይህን አንብቦ የስብሰባዉን ሰአት ለመለወጥና ህዝቡ ስብሰባዉን ገብቶ እንዳያዳምጥ
ለማድረግ እየተወያዩ መሆኑን ሰምተናል።
የሄ ቦርድ አይጥና ድመት ይመስል እዉነትን ክህዝቡ ለመደበቅ መሯሯጡን መቸ ያቆም ይሆን?
ለያንዳንዱ ሰዉ የተለያየ ወሬ በመፍጠርና በማሰራጨት ህዝቡን እርስ በራሱ እንዳይተማመንና
እንዳይቀራረብ ማድረግን የእለት ከእለት ዋና ተግባሩ እድርጎ ይዞ ቤተ ክርስቲያኑን ወደ ጥፋት
ጎዳና እየመራ ነዉ።
ከዚህ ይልቅ ህዝቡን ሰብስቦ ላደረሰዉ ጥፋት ይቅርታ መጠየቅና ንስሃ መግባት ይሻለዉ ነበር።
የክርስትና እምነታችንም የሚያዘዉ ይህንን ነዉ።
ቦርዱ ግን ክዚህ ይልቅ ካድሬ ይመስል እየዋሸ መሞትን መርጧል!!
ስለዚህ እኛ ምእመናን ይሄንን እየተከታተልን በስብሰባዉ መሳተፍ ይኖርብናል።
የሚወደኝ ህጌን ይጠብቃል ዮሓንስ 10፡15
ህዝበ ክርስቲያን ሆይ መቅደስ ሲደፈር ሰምተህ እንደት ዝም ትላልህ?
ቦርዱ መቅደስ ዉስጥ በመቋሚያና በመስቀል የሚማታ ካህን አቅፎ ይዟል።
ያስተዳድረኛል ብለህ የመረጥከዉ ቦርድ የቀጠረዉ ካህን ከታቦቱ ጋር እንድህ ሲዳፈር ሰምቶ
አንዳልሰማ፤ አይቶ እንዳላየ ፤ ይህን የድፍረት ሥራ ዉጦ ዝም ብሏል።
በዚህ ግለሰብ ላይ እርምጃ ከመዉሰድ ይልቅ ካአባ ፓዉሎስ ሰወች ጋር ቤተ ክርስቲያኑን አሳልፎ
ለመስጠት በሽምግልና ስም ክሚንቀሳቀሰዉ ቡድን ጋር እየተደራደረ ይገኛል።
ምእመናን ሆይ!
መቅደሳችን እንደ ፕሮቴስታንቶች ቤተ ክርስቲያን ባዶ አዳራሽ መሆኑ ነዉ ወይ?
ድብድብ የሚካሄድበት!
እግዚኦ! አግዚኦ! አምላክ ከዚህ ስውረን! ክቁጣዉ አድነን! ወደ ማን እንጮሃለን! ማንስ
ይሰማናል!
ያላባት እንድናመልክ ፈርደዉብን የእግዚአብሄርን ልጆች በተኑን!!
ይሄዉ ዛሬ ደግሞ መቅደስ ዉስጥ የሚደባደብ ካድሬ ለቀቁብን!!
መቸ ነዉ እነዚህን ጉዶች በቃችሁ የምትሉት!!
የሚወደኝ ህጌን ይጠብቃል አሜን!!!
የእዉነት ያለህ
ቤተ ክርስቲያናችን ላይ የተሰነዘረው ጥቃት የተቀነባበረው በኢሃድግ መንግስት
ነው፡
በደካማ ጎናችን ገብቶ እያጠቃንም ነው፡ ይሕም ሊሆን የቻለው አስተዳደሩ ስራት
ያለምንም ማዕቀብና ቁጥጥር የተዋቀረ በመሆኑ ነው፡ በዚህም ምክንያት ከዉስጥና
ክዉጭ የተሞከረውን አደጋ መቋቋም አቅቶት ሲንገዳገድ ይታያል።
ባለፉት 19 አመታት የተከትልነው አስተዳደራዊ አስራር ተንዶ ለፍርድ ሸንጎ
ዳርጎናል።
ዎደፊት ለመጓዝና ይህን ብልሹ አስተዳደር ለመለዎጥ መፍትሄው፡ ግልጥ! ያለ
የአስዳደር (ትራንስፓረንሲ) ያለው አሰራር መዘርጋት ነው።
የህም ግልጥ አሰራር በሂሳብ መዝገብ አያያዛችን መጀመር አለበት የሚል ሃሳብና
ዕቅዱ ላስተዳደር ቦርዱ ቀረበ። ቦርዱ ግን ይህ የአሰራር ዘዴ ከቀረበለት ቀን ጀምሮ
ይህን እቅድ መቃዎሙን ተቀዳሚ ስራው አደረገ። ይባስ ብሎም ሃሳቡን ያቀረቡ
አባላትን ስም እየጠሩ ስራ አላሰራ አሉን በማለት የስም ማጥፋት ዘመቻን ስራየ
ብለው ተያያዙ። ለምን?
በ2007 ዓ.ም በበጎ አድራጎት ኮሚቲ አማካኝነት ዎጭ የሆነውንና እስከ ዛሪ ድረስ
ይህ ኮሚቲ ደረሰኝ ሊያቀርብበት ያልቻለውን ሰነዶች በ2008 ዓ.ም ላይ
ለመዕመናኑ መበተኑ ይታዎሳል። በዚህ ሰነድ ላይ ስማቸዉ የተዘረዘረው ግል ሰቦች
በሙሉ የዎሰዱትን ገንዘብ አባከኑት ተብሎ ክስ አልቀረበም? ይልቁንም የሰነዱ
መሰራጨት ዋና አላማ የነበረው ማህበረ ቅዱሳን በስሩ የሚተዳደሩ ቤተ
ክርስቲያናትና የራሱን የግል ስራ ለማስፈጸም በአንድ አመት ውስጥ ብቻ ስንት ብር
አንደዎሰደ ለማሳየት የተደረገ ሙከራ ነበር። ዓላማዉ በብዙ ዉጣ ዉረድ ግቡን
ሊመታ ችሏል፡ በዓንጻሩም የህ ሰነድ ዛሬ ይፋ ሆኖ ለመጣዉ ችግር ምክንያት
ሆኗል።
የአስተዳደር ቦርዱ በየሶስት ዓመቱ በሂሳብ አጣሪ (CPA) አስመርምሮ ለመዕመናኑ
የሚያሳዉቀዉን የሂሳብ ዝርዝር (ኦዲት) ማቅረብ ያቃተዉ በዚህ ለሕዝብ
በተበተንዉ ሰነድ ምክንያት ነው።
የኦዲተሩ አቀጣጠር ከመተዳደሪያ ደንቡ ዉጭ ያለምንም ጨረታ በትዉዉቅ መጥቶ
የተቀጠረ ሂሳብ ተቆጣጣሪ ነዉ። ይሄው ተቆጣጣሪ ቀደም ሲል ለቤተ ክርስቲያኑ
ተመሳሳይ አገልግሎት መስጠቱ አይዘነጋም። የሂሳብን መዝገቡ እንደምንፈልገው
በማቀነባበር አቅርብልን (COOK THE BOOK) ማለትም ዋሽልን ተብሎ ሴጠየቅ?
ሳያመነታ የደንበኞቹን ፍላጎት እንጅ የጠራ የሂሳብ የመቆጣጠር ስራ የሰራ
እይደለም።
ይኄዉ ግለስብ ባለፈዉ የአስተዳደር ቦርድ የዎጭ ሰነዶችን ደምረህ በምታገኘዉ
ቅምር ሂሳቡ እንደተዎራረደ አድርገህ አቅርብልን ብለው ቀጥረዉ እንደተጠየቀዉ
ሰርቶ በማቅረብ ኦዲት በ (C P A) ተደረገ ምንም የጎደለ ሂሳብ የለም ተብሎ
በጭብጨባ ሪፖርቱን መዕመናኑ እንዲቀበል ተደርጎ በሽፍንፍን መታለፉን
ሁላችንም እናውቃለን።
የዛሬዉም ቦርድ ይህንኑ አሰራር ለመድገም ቀና ደፋ ሲል ተደርሶበት፡ የለም ይህ
አሰራር ዖዲት ሳይሆን የዎጭ አጠቃላይ ድምር ዉጤት ነው ሲባል ልስራው
መጓተት ምክንያት ሆነ።
ዉድ መዕመናን አንድ ሰነድ ይህን ያህል የሰዉ ዓይን ክገለጸ ዎደ ኋላ የ አስር
ዓመት ሂሳብ ዖዲት ይደረግ ቢባል ዉጤቱ ምን የሚሆን ይመስላችኋል?
እኛ አባላቱ ይህን የመጠየቅ መብት የለንም ይሆን? ዎይስ ጥቅማቸዉ የተነካ
የዘራፊዎች ቡድን እንደሚያሰራጩት ዎሬ ይህን “ የፍሚጠይቁና የሚጽፉ የኛ
ሰዎች አይደሉም “ እየተባለ የኛ ሰዎች አይናቸዉን የከፈቱ አይደሉም
“ያደረግነውን ብናደርጋቸዉ የኛ የሆኑ አይቃዎሙንም” ገንዘባችንና አቅማችንን
አዋጥተን የጀመርነውን ቤት ክርስቲያን መበዝበዝ ቀርቶ መሸጥም እንችላለን እያሉ
ስለሚፎክሩ ከበይ ክፍል ያልሆነ ሁሉ የነሱ ሰዉ አይደለም ለማለት ይሆን?
እንድታዉቁልን የምንፈልገው እኛ አንዳዶቻችን ይሄ ዲርጊት በዛ ይቅር ሳያዋርደን
እናቁመዉና ዎደ መልካም ተግባር እንመለስ የምንል ነን ይሄንንም ያደረግነው
እናንተን ዘመዶቻችንና ጓደኞቻችን ትለቅ የሃፍረት ካባ እንዳትጎናጸፉ ነዉ።
በዚሁ ማስታዎሻ አማካይነት ግለጥ (ትራንስፓረንሲ) አሰራርን አብዛኛቹ የቦርድ
አስተዳደር አባላት የቀድሞዎቹም ሆኑ አሁን ያሉትና ደጋፊዎቻቸዉ ሽንጣቸዉን
ገትረው እየተቃዎሙ መሆናቸዉን እንድታዉቁ ለናንተ ለመዕመናኑ ማስረዳቱ ተገቢ
ነው፡ ይህም የሚሆንበት ምክንያት እንደ ድሮው እንደፈለግን እናደርጋለን እንጅ
ማንም እንዲቆጣጠረን አንፈልግም፡ አንዳንድ እነዙህ የኛን ሰዎች የሚነካ ጥያቄ
ሲነሳ አፍንጫ ሲነካ ዓይን ያለቅሳል እንደተባለው እኛዉ በኛዉ ተጠራርተን
እናፈርሰዋለን እንጅ ከ ዱሮው አሰራር አንዎጣም፡ ዘላለም እንደበዘበዝን አንኖራለን
እንደሚሉ ነዉ።
በሚቀጥለው እስትንገናኝ ደህና ሁኑልን።
ዎስብሃት ለዓምላክ።

Thursday, October 29, 2009

በሽምግልና ስም አይን ያወጣ ድርቅና!!!!
የፊታችን ቅዳሜ ኦክቶበር 31 2009 ዓ.ም ከቅዳሴ በኋላ ራሱን የሽማግሌ ኮሚቴ ነኝ ብሎ
የተሰባሰበዉ ቡድን ከቤተ ክርስቲያኑ የአስተዳደር ቦርድ ጋር ስብሰባ ይቀመጣል።
ስለ ቤተ ክርስቲያኑ ችግር ማወቅ የምትፈልጉ በችግሩ ዙሪያ ማን ከማን ዎገን ሆኖ
እንደሚታገልና የሽማግሌዎቹን አቋም ለማወቅ የምትሹ ሁሉ በዚህ ስብሰባ ላይ መገኘት
ይኖርባችኋል።
ማንም አባል በቦርድ ስብሰባ ላይ ተገኝቶ የመስማት መብቱ በቤተ ክርስቲያኑ መተዳደሪያ ደንብ
3፤ 8፤1 መሰረት የተጠበቀ ነዉ።
በዚህ ስብሰባ ላይ መገኘት አስፈላጊ የሚሆንበት ምክንያት ምንድን ነዉ?
1 ይህ የሽማግሌዎች ስብስብ የሚያቀርበዉን የማስታረቂያ ሃሳብ ቦርዱ ተቀብሎ ማህበርተኛዉን
ሳያማክር በስራ ላይ ለማዋል የግዴታ ዉል እንዲፈርም የጠየቀ ስለሆነ!
2 ከኦርቶዶክስ ሃይማኖት ስነ ስርአስት ዉጭ “ገለልተኝነት” የሚለዉን ሃሳብ አፍልቀዉ ዛሬ
ያለንበት ችግር ዉስጥ ያሰገቡን ስዎች ስለሚገኙበት!
3 “ገለልተኞች” የሚለዉ ሃሳባቸዉን ስራ ላይ ካዋሉ በኋላ “የካህናት እና የምእመናን ማህበር”
የሚል ድርጂት ያቋቋሙ ግለ ስቦች ስለሚሳተፉበት!
4 ይህ የካህናትና የምእመናን ማህበር የሚባለዉ ድርጅታቸዉ ቀደም ብለዉ ገለልተኞች ብለዉ ከ
አባቶች ያገለሉአቸዉን ቤተ ክርስቲያናት ባዲሱ ድርጅታቸዉ ስር አስገብቶ ለማስተዳደር ቅድመ
ዝግጅቱን የሰሩ ሰዎች ስለሆኑ!
5 የዚህ ድርጅት የዘንድሮ ስብሰባ ወጭ በመሸፈንና በማስተናገድ ሃላፊነቱን ቤተ ክርስቲያናችን
እንድትወስድ ያደረጉ ሰወች ስለሚገኙበት!
6 የዳላስ የኢትዮፕያዉያን ኮሚኒቲ ማህበር የቀድሞዉ የአመራር አባላት ስለሚሳተፉበት!
7 እነዚህ ግለሰቦች በኮሚኒቲዉ አመራር ላይ በነበሩበት ወቅት በነሱ ቁጥጥር ስር ያለዉን የሬዲዮ
ጣቢያ የኮሚኒቲዉን ችግሮች ህዝቡ እንዳያዉቅና እንዳይወያይበት ብሎም መፍትሄ እንዳያገኝ
አፍነዉ የያዙ ስለነበሩ !
8 በኮሚኒቲዉ አመራር ላይ በነበሩበት ወቅት የተለያዩ የኮሚኒቲዉን ችግሮች ከመፍታት ይልቅ
ማህበሩን የግል ስራቸዉን ማስፋፊያና የተሻለ ስራ ለመያዣ መሸጋገሪያ ድልድይ አድርገዉ
የተጠቀሙ ስወች ስለሆኑ!
9 ይህ ደብር ችግር ላይ ወድቆ ለሁለት ሲከፈል የተገነጠለዉን ቡድን ለማቋቋም በገንዘባቸዉና
በጉልበታቸዉ የረዱ ግለሰብ ስለሚገኙበት!
10 የፍሎሪዳንና የደንቨርን ቤተ ክርስቲያናት ላባ ጳዉሎስ ያስረከቡ ግለሰብ ስላሉበት!
11 ከከሳሾች ጋር ምኞትና አላማቸዉ አንድ ስለሆነ ለሽምግልና ብቃት ስለሌላቸዉ!
በኛ ግምት እነዚህ ሽማግሌወች ነን ባዮች ራሳቸዉን ተብትቦ የያዘዉን ችግርና ሃፍረት ከላያቸዉ
ለመቅረፍ ሌላ ሽማግሌ ያስፈልጋቸዋል እንላለን።
ስለዚህ ነዉ በስብሰባዉ ላይ መገኘትና የሚሉትን መስማት አለባችሁ የምንለዉ።

Friday, October 23, 2009

ዛሬ በተጨማሪ የኛ ቤተ ክርስቲያን አዎናባጆች እየሰሩ ያለዉን ትረዱ ዘንድ ይህን ጽሁፍና ትንተና እናቀርብላችኋለን.

http://www.quatero.net/pdf/Erim.pdf


%"$A? BÅ (asteraye@gmail.com)

በጥሞና ተመልከቱት

Thursday, October 22, 2009

ለቦርዱ ሊቀ መንብርና ሽምግልና እንቀመጥ እያሉ ሽር ጉድ ለሚሉት ግብረ አበሮቹቢተ
ክርስቲያናችንን ወዲት እንደሚወስዱት እንድትረዱት ከ ኢትዮሚዲያ ያገኘነዉን እናቅርብላችሁ።
http://ethiomedia.com/course/zeregnanet_bebete_kihnet.pdf


በአሜሪካ የፓትርያርኩ ዯጋፊ ካህናት ምሥጢራዊ የስልክ ስብሰባ ማዴረግ ጀምረዋል
ጠቅላይ ቤተ ክህነቱ በገባበት ምስቅልቅል እና ቅደስ ፓትርያርኩ “ተጠሪነቴ ሇቅደስ ሲኖድስ አይዯሇም፣ ሕጉንም አሻሽላሇሁ” ካለ ወዱህ እና ይህንን አንቀበልም ያለ ጳጳሳት ቤቶች የመሰበር አዯጋ ከገጠማቸው ወዱህ የወንበራቸው ነገር ያሰጋቸው ብፁዕ ወቅደስ አቡነ ጳውሎስ አዱስ ስትራቴጂ ነዴፈው በመንቀሳቀስ ላይ መሆናቸውን ምንጮቻችን አስታወቁ።
በምግባራቸውና ኦርቶድክሳዊ ባልሆነ አስተዲዯራቸው ከምዕመኑና ከአባቶች ፍቅርን የተነፈጉት ቅደስ ፓትርያርኩ ቤተ ክርስቲያንን የሚመዘብሩ “የማፊያ” ቡዴን አባላትንና ዘመድቻቸውን በመያዝ ተቃውሞ እየገጠማቸው ያሇው በዘራቸው ምክንያት መሆኑን ሇማሳየትና የትግራይን ክርስቲያን ሕዝብ ዴጋፍ ሇማግኘት በመጣር ላይ ናቸው። አባ ሰረቀ ብርሃን ወልዯ ሳሙኤል በተባለትና በአሜሪካን ሀገር “በትግርኛ ብቻ ነው ማገልገል የምፈልገው” በሚል ዘዬ ትግርኛ ተናጋሪው በሌላው ሕዝበ ክርስቲያን እንዱጠላ ካዯረጉት ሰዎች አንደ በሆኑት ግሇሰብ ተባባሪነት በመንቀሳቀስ ላይ ባሇው በዚህ አዱስ ታክቲክ በአሜሪካ ያለ የፓትርያርኩ ዯጋፊ መነኮሳት፣ ካህናትና አንዲንዴ በቤተ ክርስቲያን ዙሪያ ያለ ሰዎች ሇብቻቸው በስልክ ኮንፈረንስ እንዱሰበሰቡና አቋም እንዱይዙ እየተዯረገ መሆኑ ታውቋል።
ከዚህ በፊት በጠቅላይ ቤተ ክህነት ይሠሩ በነበሩ ሰው አስተባባሪነትና መሪነት እየተካሄዯ ባሇው በዚህ “የፓትርያርኩ ዯጋፊ ካህናት ልዩ ምሥጢራዊ ስብሰባ” ላይ እየተወሳ እንዲሇው ከሆነ ፓትርያርኩ ተቃውሞ እየገጠማቸው ያሇው በአስተዲዯራቸው ዯካማነት እንዲልሆነ ስምምነት አሇ። ከዚህ ተቃውሞ ጀርባ ያሇው ዯግሞ በዚያው በጠቅላይ ቤተ ክህነቱ ውስጥ ያሇው ማህበረ ቅደሳን የተባሇው ማህበር በመሆኑ በተሇይ በአሜሪካ ዯረጃ የዚህ ማህበር አባላት የሆኑትን ሰዎች ጠራርጎ ማስወጣት እንዯሚገባ ውይይት ተዯርጎበታል።
ማህበረ ቅደሳን “ፓትርያርክ ጳውሎስን በማውረዴ የራሱን ሌላ ፓትርያርክ መሾም ይፈልጋል” የሚለት እነዚሁ ግሇሰቦች ቀዯም ብሎ በአንዲንዴ የአሜሪካ አብያተ ክርስቲያናት በነ አባ ወልዯ ትንሳኤና ተከታዮቻቸው እንዯተዯረገው ዓይነት “የማህበረ ቅደሳን አባላትን የማባረር ዘመቻ” መጀመር እንዯሚገባ ተወያይተዋል። በስብሰባው ላይ ከነበሩት መነኮሳት መካከል ጥቂቶቹ (ሇጊዜው ስማቸውን መጥቀስ አልፈሇግንም) “አሁን ይህንን ሇማዴረግ እንቸገራሇን፣ ባይሆን ሇወዯፊቱ እናስብበታሇን” ያለ ሲሆን በተቃውሞ የቀረቡ ግን አሇመኖራቸው ታውቋል። አንዴ ካህን ብቻ “እስካሁን አብራችሁዋቸው ኖራችሁ አሁን ሇምን ታባርራችሁዋላችሁ። ስንት አገልግሎት የሰጧችሁ እነርሱ አይዯለም ወይ?” ሲለ መጠየቃቸው ተሰምቷል።
ማህበረ ቅደሳን በአሜሪካ የሚገኙ አብያተ ክርስቲያናትን “ወዯ እናት ቤተ ክርስቲያን ካልገባችሁ” እያሇ ሲወተውት በመኖሩ ከብዙዎች ቂም ማትረፉ ይታወቃል። ሀገር ቤት ያሇው አስተዲዯር “ገነት” የሆነ ይመስል “ሀገር ቤት ያሇው አስተዲዯር ወይም ሞት” ሲል የነበረው ማህበረ ቅደሳን አሁን እርግጫና ደላ ሲገጥመው አቋሙን ይቀይር ይሆናል የሚል አስተያት አሇ። ግማሹን ገሇልተኛ፣ ግማሹን ስዯተኛ እያሇ ከአቡነ ጳውሎስ አስተዲዯር ጋር የሙጥኝ ብሎ የከረመው ማህበረ ቅደሳን አሁን አባላቱ “በሀገር ቤቱ አስተዲዯር ሥር ካለ አብያተ ክርስቲያናት የሚባረሩ ከሆነ ከሁሇት ያጣች ጎመን” የመሆን ክፉ ዕጣ ይገጥመዋል ማሇት ነው።
ማህበረ ቅደሳን ሕዝብ ገሇል ያዯረጋቸውንና “የወያኔ አብያተ ክርስቲያናት” የሚባለ አብያተ ክርስቲያናት የሁለም ሕዝበ ክርስቲያን መሆናቸውን ሇማሳየት አባላቱን በውዳታ ግዳታ ወዯነዚህ ቦታዎች እንዱሄደ ሲመራ መቆየቱ ታውቋል።
ከነዚህም አብያተ ክርስቲያናት መካከል በሎስ አንጀሇስ የቅዴሰት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን፣ በዱሲ የአቡነ ማቲያስ መዴሃኔዓሇም፣ በአትላንታ ጽዮን ማርያም፣ በሜኖሶታ ማርያም፣ በሲያትል የቅደስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን እና በዲላስ የተ/ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን እንዯሚገኙበት ተጠቁሟል። ይህንን ሁለ አዴርጎ፣ አባላቱ በገንዘባቸው ቦታዎቹን ካቋቋሙ በኋላ አሁን እንዯ ወንጀሇኛ እንዱወጡ ምክር መጀመሩ በጣም እንዯሚዯንቅ ነገሩን የመረመሩ ምንጮቻችን ተናግረዋል።

Wednesday, October 21, 2009

ቤተ ክርስቲያናችንን እናድን እያልን እንማጠናለን!!!!
የዚህ ደብር መዕመን እግዚአብሄርን የምንፈ-ራ ዓምላካችንን የምንወድና የምንታዘዝ ነን! ትሁት
ልቦናችንን አይቶ በጥገኝነት ከምናመልክበት ቤት አዉጥቶ ዛሬ ይህን ትለቅ ሕንጻ የሰጠን
አምላካች ስሙ ለዘላለም የተመሰገነ ይሁን።
መዕመኑ በመላእክትና በጻድቃን ስም ዙሪያ ተሰብስበዉ ይዘክራሉ ይጽልያሉ የበረከቱ ተሳታፊ
ለመሆን እንሽቀዳደማለን ደስ የሚል የክርስትና ሕይወት ነዉ።
በዚህ መንፈስ ለረጅም ዘመን አብሮ ዓማላክን በማምለክ በተመሰረተ ግንኙነት ብዙወቻችን
በጋብቻ በአበልጅነት ዝምድና ፈጥረናል ከሌሎቻችንም ጋር ጥለቅ ወዳጅነትን መስርተናል።
የዚህ ሁሉ መሰረት እያንዳንዱ ግለሰብ ለዓምላኩና ልኃይማኖቱ ባለዉ ፍቅር ሳቢያ የተፈጠረ
ወዳጅነት ነዉ። የተቀረዉ ግንኙነት በዚህ ጽኑ ዓላማ ዙሪያ የተገነባ ክርስቲያናዊ ማሕበራዊ
ህይወት ነዉ።
ከኅዋሪያት መሃል ይሁዳ ጌታን ክዶ እንደሸጠዉ እናዉቃለን። ከኛም መሃከል ለአገልግሎት
መርጠናቸዉ ለጥቅማቸዉ ሲሉ እኛ ዎደማንፈልገዉ አቅጣጫ ልወስዱን እየሞከሩ ያሉትን
ዎንድሞቻችንና እህቶቻችን የመጨረሻዉን ጥፋት ክመፈጸማቸዉ በፊት ማቆም አለብን።
እምነታችን ክማንም በላይ መሆኑን የምናሳይበት ሰዓት ዛሬ ነዉ።
አባ ፓዉሎስ ወያኔ ናቸዉ። ስለዚህም ነዉ ሓገር ቤት ያለዉ ወገናችን ያልተቀበላቸዉ። ባገኘዉ
አጋጣሚ ሁሉ ተቃዉሞዉን እየገለጸ የሚገኘዉ። እርሳቸዉም ክዚህ የተነሳ እንደ አንድ አምባ
ገነን መሪ በደረሱበት ሁሉ በመከላከያ ሰራዊት አባላት የሚጠበቁት።
ሥራቸዉንም የሚሰሩት በሕዝብ ደህንነት ዓባላት ታጅበዉ ነዉ።
ነጻነቱን የተነጠቀዉ መብቱ የተረገጠዉ የሃገራችን ጀግና ህዝብ ይህ ሁሉ ችግር ሳይገታዉ እኝህን
አባት ጥግ ይዘው እንዲንቀሳቀሱ አድርጓል።
እኛ በነጻነት የምንኖር ያለምንም ስጋት ሃሳባችንን መናገር የምንችል ወገኖች ግን የኛዉ ናቸዉ
ይምንላቸዉ ጉዶች ለዚህ አባት አሳልፈዉ ሊሰጡን በከፍተኛ ፍጥነት ሲንቀሳቀሱ በግልጽ እየታየ
በፈጠርነዉ ማህበራዊ ኑሮ እርምርጃ ላንወስድ በይሉኝታ ታስረን እንገኛለን።
ከዕምነታችን ይልቅ ወዳጅነታችንን አስቀድመን ወደ ጥፋት ጎዳና እየተጓዝን ነዉ።
ይህ ዝምታችን የሚያበቃዉ መቸ ነዉ?
የቦርዱ ሊቀ መንበር ሰሞኑን ላባ ፓዉሎስ የጻፈዉን ደብዳቤ እንዳነበባችሁ እርግጠኞች ነን፡
ጥቂቶቻችሁም ለሰላም ሲባል የተጻፈ ጥሩ ደብዳቤ ነዉ ስትሉ ተሰምቷል።
ዉድ መዕመን ሆይ! ፋሽስት ሙሶሎኒ ሃገራችንን ሲወር ትምህርት ቤት እከፍታለሁ ሆስፒታል
አቋቁማለሁ መንገድ እዘረጋለሁ ህዝቡን ነጻ እደርጋለሁ ብሎ ነበር ሲከራከር የነበረዉ፡
እንድም ቀን ባሪያ አድርጌ ቀጥቅጨ ልገዛ ነው ብሎ አልተነፈሰም።
ዲያብሎስም ጌታን ሲፈታተን የዓለምን መንግስት ሁሉ ከነ ክብራቸዉ እሳየዉና “ ተንበርክከህ
ብትሰግድልኝ ይህን ሁሉ እሰጥሃለሁ” አለዉ ማቴዎስ 4፡8-9 ይሁዳ አሳልፎ ሲሰጠዉ ሰይፍ
የያዙት ሰራዊት ክኋላ ተደበቀዉ እርሱ ግን “መምሕር ሆይ! ሰላም ላንተ ይሁን” በማለት ነበር
የቀረበዉ ማቴዎስ 26፡49
የኛም ሊቀ መንበር የጻፈዉ ደብዳቤ ዉስጡ ሲታይ ጉዱ ብዙ ነዉ “እኛ በዓለሙ ሁሉ
ተሰራጭተን የምንገኝ ተባባሪዎች” እያለ የሳቸዉ ተወካይ መሆኑን በደብዳቤዉ መግቢያ ላይ
ገልጾታል።
501፡ c ፈቃድ ያለው ድርጂት አቋቁመዉ ገንዘብ እየሰበሰቡ ነዉ።
ቤተ ክርስቲያናችን ዛሬ ከፍተኛ አደጋ ላይ ነች፡ ሁሉም ሊቀራመትዋት ክበዋታል! የዓምላክን
ጥሪ ተቀብሎ የሚመራ ሰዉ ትፈልጋለች።
ነገሩ ካለቀ በኋላ መጸጸት ፋይዳ የለዉም!
በህብረት ተነስተን ቤተ ክርስቲያናችንን ከነዚህ ቡድኖች መንጋጋ እናዉጣ!!!
እግዚአብሄር ይርዳን።

Monday, October 19, 2009

ዘግይቶ የደረሰን አብይ ዜና
የቦርዱ ሊቀ መንበር በአባ ፓዉሎስ ለሚመራዉ ሲኖዶስና ለወያኔው ፓትሪያርክ ላባ ፓዉሎስ
የጻፈዉን ደብዳቤ እንድታነቡት እናቀርብላችኋለን።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ዓለም አቀፋዊ የምእመናን ማሕበር
WORLD ASSOCIATION OF PARISHIONERS OF THE ETHIOPIAN ORTHODOX TEWAHEDO CHURCH
10107 Branwood Circle, Dallas, TX 75243, U.S.A. WWW.eotcipc.org
Tel: (469)855 8488 (214)697 8928; (813)312 1502; e-mailmiimenan@yahoo.com
መስከረም 18 ቀን 2002 ዓ/ም
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ፤ አሐዱ አምላክ፤ አሜን።
ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን
ቅዱስ ሲኖዶስ፤
ለብፁዕ ወቅዱስ ፓትሪያርክ
ለብፁዓን የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት
አዲስ አበባ።
ጉዳዩ፤ በቤተክርስቲያናችን፤ ሰላም፤ አንድነትና ዘላቂ እድገት እንዲገኝ ስለ ማድረግ፤
በመጀመሪያ፤ ለቅዱስ ሲኖዶሱ ያለንን እጅግ ከፍ ያለ አክብሮት እየገለጽን፤ ለብፁዓን የቅዱስ ሲኖዶሱ አባላት
የእግዚአብሔር ሰላምታችንን በትሕትና እናቀርባለን።
እኛ በዓለሙ ሁሉ ተሰራጭተን የምንገኝ ተባባሪዎች የቤተክርስቲያናችን ምእመናን በቅርቡ በቅዱስ ሲኖዶሱ
አባላት መሀል በተከሰተው ውዝግብና ባጋጠሙት ድርጊቶች እጅግ ተሳቅቀናል፤ አዝነናልም። ሆኖም፤ በጥቅምት
ወር 2002 ዓ/ም የቅዱስ ሲኖዶሱ ስብሰባ ስለሚከናወን ጉባኤው ለቤተክርስቲያናችን የተሙዋላ ሰላምና አንድነት
እንዲያስገኝና የዘለቄታ እድገት የሚያመቻች ስልት እንዲተልም የበኩላችንን ግንዛቤና ማሳሰቢያ ከዚህ በታች
በአክብሮት እናቀርባለን። የቅዱስ ሲኖዶሱ ጉባኤም በቤተክርስቲያናችን ላይ ተጋርጠው የሚገኙትን እጅግ ከባድ
ችግሮች ለማስወገድ ተገቢ የሆኑ መፍትሔዎችን እንደሚያስገኝ ያለንን ፅኑ ተስፋ በቅድሚያ እንገልጻለን። ስለዚህ፤
ቅዱስ ሲኖዶሱ፤ በመንፈስ ቅዱስ መሪነት፤ ከዚህ በታች የምናቀርባቸውን ሀሳቦች በጥሞና ተመልክቶ ቅድስት
ቤተክርስቲያናችንን ለዘለቄታ በሚያጠናክርና በሚያስፋፋ ስልት ተገቢውን ውሳኔ እንዲያደርግ እንማጸናለን።
1. ስለ ቅዱስ ሲኖዶሱ ሥልጣን፤
እንደሚታወቀው፤ በ1991 ዓ/ም በቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ የተደነገገው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን
ሕገ ቤተ ክርስቲያን አንቀጽ 5 የቅዱስ ሲኖዶስን ሥልጣን እንደሚከተለው በግልጽ አስቀምጦታል፤
“1. በመንፈስ ቅዱስ የሚመራው ቅ/ሲኖዶስ የመንበረ ሐዋርያት ወራሽ ስለሆነ በቤተ ክርስቲያኒቱ
የመጨረሻው ከፍተኛው ሥልጣን ባለቤት ነው።
2. ከማንኛውም የቤተ ክርስቲያኒቱ የሥልጣን መዋቅር ሁሉ የበላይ አካል ቅዱስ ሲኖዶስ ስለሆነ
ሕጎችን፤ ልዩ ልዩ ደንቦችንና መመሪያዎችን የማውጣትና የዳኝነት ሥልጣን አለው።”
2
ከላይ በሁለቱ ንኡስ አንቀጾች እንደተገለጸው፤ የቅዱስ ሲኖዶስ ሥልጣን በማያሻማ ሁኔታ በግልጽ የተደነገገ ስለሆነ
በቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ ወቅት በወገናዊነትም ሆን በዓለማዊ ጥቅም ፍለጋ ምክንያት በማንም የውጪም ሆነ የውስጥ
አካል ተጽእኖ እንዳይሸረሸርና እንዳይዛባ በእግዚአብሔር ስም ከፍ ባለ ትሕትና እንጠይቃለን።
2. ስለ ሰላምና አንድነት፤
በአባቶቻችን መካከል የተፈጠረው አለመግባባትና መከፋፈል አደባባይ ወጥቶ መዘባበቻ በመሆኑ በአባቶቻችን ላይ
በቀላሉ የማይፋቅ ታሪካዊ ትዝብት ያተረፈላቸው መሆኑ ግልጽ ነው። ይህ ሁኔታ ቤተ ክርስቲያናችንን እጅግ
በሚያሰጋና በሚያሳስብ ሁኔታ አደጋ ላይ ጥልዋታል። ይህ በአባቶች መካከል የተከሰተው መከፋፈል፤ መኖቆርና
አንድነት ማጣት፤ በአመራር ደረጃ የሚታየው ግዴለሽነትና ብቃት ማጣት፤ ምእመናንን ግራ ያጋባው ስደተኛ
ሲኖዶስ በመባል ያስከተለው መወጋገዝና የቤተ ክርስቲያናችን መከፋፈል አዝማሚያ መታየት እነዚህና ሌሎችም
ሁኔታዎች ለቤተ ክርስቲያናችን ጠላቶች መጠናከርና መስፋፋት አመች ሁኔታ ፈጥሮላቸዋል። ስለዚህ የቅዱስ
ሲኖዶስ አባላት እነዚህን ለቤተ ክርስቲያናችን በጣም አደገኛ የሆኑትን ክስተቶች በማጤንና በማሰላሰል፤
በክርስቲያናዊ አስተሳሰብና ይቅር ባይነት በመካከላችሁ የተፈጠረውን አለመግባባትና መከፋፈል አስወግዳችሁ
በፍጹም ፍቅርና ሕብረት በመወያየት ቤተ ክርስቲያናችንን ከተጋረጡባት አደጋዎች እንድታድኑዋት በጌታችን፤
በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስና በእናቱ በቅድስት ድንግል ማርያም ስም ከፍ ባለ ትሕትና እንማጸናችሁዋለን።
3. ስለ አስተዳደር ጉድለት፤
በባለሙያ የተጠና መዋቅር፤ ግልጽና የማያሻማ የአስተዳደር ደንብ፤ ዓላማው ግልጽ የሆነ የአጭር፤ የመካከለኛና
የረዥም ጊዜ እቅድ የሌለው ማንኛውም ተቁዋም፤ ብክነት፤ ሙስና፤ አድልዎ፤ የሥራ ቅልጥፍና ማጣትና
የመሳሰሉት የአስተዳደር ብልሹነት የሚታይበት መሆኑ አያጠራጥርም። ቤተ ክርስቲያናችንንም እዚህ ምስቅልቅልና
አደጋ ላይ ጥሎ ለውድቀት ከዳረጉዋት ምክንያቶች ውስጥ አንዱ ይህ ሁኔታ መሆኑ እውነት ነው። በተለይ እንደ
ቤተ ክርስቲያናችን ያለ ግዙፍ ተቁዋም በየመስኩ በሚገኙ ባለሙያዎች የተጠና መዋቅር፤ በመዋቅሩ ላይ
የተመሠረተ ግልጽና የማያሻማ የአስተዳደር ደንብ፤ በቤተ ክርስቲያኒቱ ዓላማዎች ላይ የተመሠረተ የአጭር፤
የመካከለኛና የረዥም ጊዜ ጥርት ያሉ እቅዶችና በእቅዶቹ ላይ የተመሠረቱ ምእመናንንና ምእመናትን በሰፊው
የሚያሳትፉ የሥራ ፕሮግራሞች በባለሙያዎች ተጠንተው እንዲዘጋጁ ማድረግ ቤተ ክርስቲያናችንን ከውድቀት
ለማዳን አማራጭ የማይገኝለት ጉዳይ መሆኑ ሊታወቅ ይገባል። ስለዚህ ቤተ ክርስቲያናችን ትክክለኛውን አቅጣጫ
ይዛ በመጉዋዝ እየተስፋፋችና እየተጠናከረች በመሔድ በሕገ ቤተክርስቲያናችን በአጠቃላይ የተደነገጉትን
መንፈሳዊውንና ዓለማዊውን ዓላማዎቹዋን ግብ ለማድረስና ከገጠሙዋት ችግሮች መላቀቅ እንድትችል እላይ
በጠቀስናቸው አማራጭ በማይገኝላቸው ጉዳዮች ላይ የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ ሥርነቀል
ውሳኔ እንዲያስተላልፍ
በማክበር እናሳስባለን።
4. ስብከተ ወንጌልን ስለ ማጠናከርና ስለ ማስፋፋት፤
በሕገ ቤተ ክርስቲያናችን እንደሚከተለው ተደንግጉዋል፤
አንቀጽ 7 ቁጥር 7 “የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት በአገር ውስጥና በውጭ አገር እንዲስፋፋ
ያደርጋል።”
ነገር ግን፤ ከላይ በተጠቀሰው ሕገ ቤተ ክርስቲያን መመሪያ መሠረት የተወሰደው እርምጃ እጅግ አነስተኛ ነው።
እንደሚታወቀው፤ በአገራችን በኢትዮጵያ የቤተ ክርስቲያናችን ምእመናንና ምእመናት ስለ እምነታቸው በቂ
ትምሕርት ስለማያገኙ በብዛት ወደ ሌሎች እምነቶች እየፈለሱ በመሔዳቸው የቤተ ክርስቲያናችን እምነት
ተከታዮች ቁጥር እየቀነሰ ከመሔዱም በላይ በተለይ በገጠሩ የሚኖሩት ምእመናን ስለ ወንጌልም ሆነ ስለ
እምነታችን ያላቸው ግንዛቤ እጅግ አነስተኛ መሆኑ የታወቀ ነው። በአንጻሩ፤ የሌሎች እምነት ተከታዮች ቁጥር
እየጨመረ መሔዱ ብቻ ሳይሆን እያንዳንዱ የሌላው እምነት ተከታይ እምነቱን እንዲቀበል በስልት ተምሮ
የተቀበለውን እምነት በጣፈጡ ቃላት ለእኛው እምነቱን ያስተማረው ለሌለውና ለማያውቀው ምእመን እየሰበከ
ባል ሚስቱን፤ ሚስት ባልዋን ሲያስኮበልሉ ይታያሉ። ከኢትዮጵያ ውጪ በመላው ዓለም ተሰራጭተው በሚገኙ
ኢትዮጵያውያን ጥረትና በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንም ፕሮግራም በውጭ ሐገሮች በብዛት
3
በተቁዋቁዋሙት አብያተ ክርስቲያናት የሚገኙ ካሕናት የቅድስት ቤተ ክርስቲያናችንን እምነት በይፋ ለሌሎች ዜጎች
ስለማያስተምሩ ቤተ ክርስቲያናችን ብዙ የሌሎች ዜጎች ምእመናንንና ምእመናትን አባል ማድረግ ስትችል
የሚያስተምራቸው ስለሌለ እምነታችንን የተቀበሉ የውጭ ሐገር ዜጎች በጣም ጥቂት ናቸው። ስለሆነም፤ ከላይ
የተጠቀሰውን ችግር ቀስ በቀስ ማስወገድና ስብከተ ወንጌልን በስፋት እያሰራጩ ኢትዮጵያውያንና የውጭ ዜጎች
ምእመናንና ምእመናትን ቁጥር ማብዛት የሚቻልበት ዘዴዎች በቅዱስ ሲኖዶስ አባላት ዘንድ የሚታወቁ ቢሆንም
ለመጠቆም ያህል የወንጌል መልእክተኞቻችን በሐገራችን ቁዋንቁዋዎችና በሌሎች ዜጎች ልዩ ልዩ ቁዋንቁዋዎች
በብዛት ማሠልጠንና እንደ ሌሎቹ እምነት አስተማሪዎች በየገጠሩ በቤተ ክርስቲያን ብቻ ሳይሆን በየመንደሩ
እየተዘዋወሩ እንዲያስተምሩ ማድረግ፤ በመጻሕፍት ብቻ ሳይሆን በቀላሉ የሚነበቡ በራሪ ወረቀቶችን በልዩ ልዩ
ቁዋንቁዋዎች በብዛት እያዘጋጁ ማሰራጨት፤ በመገናኛ ብዙኅን ማለት በሬዲዮ፤ በቴሌቪዥን፤ በድረገጽና
በመሳሰሉት ትምሕርተ ወንጌልን፤ እምነታችንና ቀኖናችንን ማሰራጨት ስለሚቻል ቅዱስ ሲኖዶስ በዚህ አስፈላጊና
አሳሳቢ ጉዳይ ላይ ውይይት አድርጎ አመርቂ ውሳኔ እንደሚያስተላልፍ እናምናለን።
5. ደብሮችንና ገዳሞችን ስለ መርዳት፤
ከደርግ ዘመን ጀምሮ፤ ቤተክርስቲያናችን አብዛኛውን ንብረቷን ስለ ተዘረፈች ብዙ ደብሮችና ገዳሞች ችግር ላይ
ይገኛሉ። በብክነት ምክንያት፤ ከምእመናን የሚገኘውም በትክክሉ እንዲደርሳቸው አልተደረገም። በተከሠተው
መናቆር ምክንያትም፤ ውጪ ሐገሮች ያሉት ምእመናንም በሚችሉት መርዳት አልቻሉም። በተጨማሪም፤ እጅግ
አሳሳቢ ሆኖ የቆየው፤ ታሪካዊው የኢየሩሳሌሙ “ዴር ሡልጣን” (1) ገዳማችን የሚያስፈልገው ጥገና
ስላልተከናወነለት የመፍረስ አደጋ ላይ ነው። ስለዚህ፤ ቤተክርሲቲያናችን ካላት ገቢ፤ ደብሮችና ገዳሞች ተገቢውን
ድርሻቸውን እንዲያገኙ፤ ለዘለቄታውም ራሳቸውን እንዲችሉ ተገቢ በሆነ ሥልት እንዲጠቀሙና፤ ከውጪም
የሚገኘው ድጋፍ እንዲዳብር፤ የእሥራኤል መንግሥትም የኢየሩሳሌም ገዳማችን እንዲጠገን ፈቃዱ እንዲሆን፤
ቅዱስ ሲኖዶሱ ተገቢ የሆነ ጠንካራ ሥልት አዘጋጅቶ ሥራ ላይ እንዲያውል በማክበር እናሳስባለን።
6. ስለ ትምህርት ማስፋፋትና ማጠናከር፤
ስለ ቅዱስ ሲኖዶስ የወጣው ሕገ ቤተክርስቲያን፤ አንቀጽ 7 ስለ “የቅዱስ ሲኖዶስ ሥልጣንና ተግባር”½
እንደሚከተለው ደንግጓል፤
ቁጥር 8፤ “የክርስቶስን ወንጌለ መንግሥትና ቀኖና ቤተ ክርስቲያንን ያስተምራል ያስፋፋል።”
ሆኖም፤ ቤተክርስቲያናችንን ካጋጠሟት እጅግ ከባድ ችግሮች አንዱ የአብነት ትምሕርት ቤቶች መዳከም ነው።
ቀድሞም ሆነ በአሁኑ ዘመን፤ የአብያተ ክርስቲያናችን ሕልውና መሠረት የአብነት ትምህርት ቤቶች መሆናቸው
ይታወቃል። ገዳማትንና አድባራትን የሚያገለግሉት ካህናት ምንጭ የአብነት ትምህርት ቤቶች ናቸው። የብፁአን
ወቅዱሳን ፓትሪያርኮች፤ የብፁአን ሊቃነ ጳጳሳትና ኤጲስ ቆጶሳት ምንጭ የአብነት ትምሕርት ቤቶች ናቸው።ስለዚህ
የእነዚህ አብነት ትምህርት ቤቶች መዳከም ማለት የቤተ ክርስቲያን መዳከም ማለት መሆኑ እውነት ነው።
ከአስተዳደር ችግሩ በተጨማሪ የገጠሬው ምእመን በከፋ ድሕነት ስለሚሰቃይ ለቆሎ ተማሪውና ለአስተማሪው
የተለመደ ቸርነቱን ሊያበረክትለት አልቻለም። ለጋሽ የነበረው የኢትዮጵያ ገበሬ ተመጽዋች በመሆኑ የቆሎ
ተማሪዎችና መምህራኖቻቸው የእለት ጉርሳቸውንና የዓመት ልብሳቸውን ከገበሬው በምጽዋት ማግኘት ስላልቻሉ
ወደየከተማው በመሰደድ ላይ ናቸው። በዚህ ምክንያት፤ የቤተክርስቲያናችን ምንጭ የሆኑት የአብነት ትምሕርት
ቤቶች አስጊ ሁኔታ ላይ ይገኛሉ። ውጪ ሀገሮች ላሉት ምእመናንም ተገቢ የሆኑ የሥልጠና ማእከሎች
(1) ማሕበራችን ስለ ታሪካዊው የኢየሩሳሌም ገዳማችን ለእስራኤል መንግሥት ጠቅላይ ሚኒስትር የሚያቀርበውን
አቤቱታ በዓለምአቀፍ
ደረጃ በማስፈረም ላይ መሆኑን የሚያሳየውንና ያሰራጨውንም መግለጪያ በድረገጹ
በwww.eotcipc.org½ይመልከቱ።
4
ስላልተቋቋሙላቸው በቤተክርስቲያናችን ትምሕርት የጠለቀ እውቀት ሊያገኙ አልቻሉም። ስለዚህ፤ የአብነት
ት/ቤቶች እንዲጠናከሩና ውጪ ሐገሮችም የቤተክርስቲያናችን ት/ቤቶች እንዲቋቋሙ፤ ቅዱስ ሲኖዶሱ ለጉዳዩ ልዩ
ትኩረት በመስጠት በባለሙያዎች ጥናት ላይ የተመሠረት ዘላቂ መፍትሔ እንዲያስገኝለት በትሕትና እናሳስባለን።
7. አክራሪዎች ስላደረሱት ጥቃት፤
ቤተክርስቲያናችንን ካጋጠሟት እጅግ መራርና አስቆጪ ጥቃቶች አንደኛው አክራሪ እስላሞች ካሕናትንና
ምእመናንን አሰቃቂ በሆነ መንገድ መጨፍጨፋቸው፤ ደብሮችንና ገዳሞችን ማቃጠላቸውና ከጠላት ሐገሮች
በሚያገኙት ገንዘብ ቤተክርስቲያናችንን በብዙ መንገድ መፈታተናቸውን መቀጠላቸው ነው። በተለይ በ1997 እና
1998 ዓ/ም ከምሥራቅ ሐረርጌ ክፍለ ሐገር ጋራሙለታ ጀምሮ በምዕራብ እስከ ኢልባቦርና ከፋ ክፍላተ ሐገራት
ባሉት አገሮች በባሌና አርሲ ብዙ አብያተ ክርስቲያናት የፈረሱና የተቃጠሉ፤ ብዙ ካህናት የተሰየፉ፤ እንደ እንስሳ
የተቀሉ፤ ተገድደው የሰለሙ መሆናቸው ያደባባይ ምሥጢር ነው። ስለዚህ ሁሉ ግፍ፤ በቤተክርስቲያናችን አመራር
ምን እንደ ተከናወነና ምን ክትትል በመደረግም ላይ እንዳለ የሚታወቅ ነገር የለም። የተከናወነው አሰቃቂ ግፍ
ተጀመረ እንጂ ያበቃለት አለመሆኑን፤ እንዲያውም የባሰ ጥቃት ሊከሰት እንደሚችል አውቆ፤ ነቅቶ እንዲጠብቅ
ለቤተ ክርስቲያናችን ምእመናን በሰፊው ማስገንዘብ ያስፈልጋል። ስለዚህ፤ ቅዱስ ሲኖዶሱ ይህን ከባድ ጉዳይ
በዝርዝር በማጥናት ተገቢው ሕጋዊ እርምጃ እንዲወሰድ እንዲሁም ቤተክርስቲያናችን ለራሷ ብቁ፤ ለዘመኑ አመች
የሆነ ሕጋዊ መከላከያ እንዲኖራት ለማድረግ የሚያስችል ሥልት አዘጋጅቶ ሥራ ላይ ማዋል የሚያስፈልግ መሆኑን
በአክብሮት እናሳስባለን።
8. ስለ ድሕነት፤
ከላይ በተጠቀሰው ሕገ ቤተክርስቲያን፤ አንቀጽ 6 ቁጥር 6 አንደኛው የቅዱስ ሲኖዶስ ዓላማ እንደሚከተለው
ተገልጿል፤
“የሰው ዘር ሁሉ ከርሃብ፤ ከእርዛት፤ ከበሽታና ከድንቁርና ተላቆ በሰላምና በአንድነት በመተሳሰብና
በመረዳዳት በመንፈሳዊ ሕይወት እንዲኖር ማስተማርና መጸለይ፤”
የሐገራችን ሕዝብ እጅግ በከፋ የድሕነት አረንቋ ፍዳውን እያየ መሆኑ የታወቀ ነው። ቤተክርስቲያናችንንም
ለእምነቱ መጠጊያ፤ ለረሐቡም ማስታገሺያ እንድትሆንለት ይፈልጋል። በዚህ ረገድ፤ ቤተክርስቲያናችን ለደኸየውና
ለታረዘው ወገናችን በበለጠ ሁኔታ ደራሽ እንድትሆን ተገቢ ሥልት እንዲቀየስና ሥራ ላይ እንዲውል፤ ቅዱስ
ሲኖዶሱ አስፈላጊውን እርምጃ እንዲወስድ በትሕትና እናሳስባለን።
9. መደምደሚያ፤
ከላይ የዘረዘርናቸው ጉዳዮች የቅዱስ ሲኖዶስ አስቸኩዋይ ትኩረት የሚገባቸው መሆኑ ቢታወቅም፤ ምእመናን
መፍትሔ የሚሹባቸው ሌሎች ችግሮችም አሉ። ከነዚህ ውስጥ ጥቂቱን ለመጥቀስ፤ (ሀ)ቃለአዋዲውን
ስለ
ማሻሻል፤ (ለ) መጠናት ስለሚገባቸው ድርሳናት፤ ገድላት፤ ውዳሴያትና ታምራት፤ (ሐ) የምእመናትን ተሳትፎ ስለ
ማጠናከር፤ (መ) ቅዱስ ቁርባኑን ባለመቀበል፤ አብዛኛዎቹ ምእመናንና ምእመናት በቅዳሴያችን በግልጽ እንደ
ተቀመጠው፤ የእግዚአብሔርን ሕግ አፍራሾች ሆነን ስለ መገኘታችን፤ ወዘተ ይገኙበታል።
ቅዱስ ሲኖዶሱ መልካም ፈቃዱ ሆኖ፤ ከላይ የዘረዘርናቸውን ጉዳዮች በጥሞና ተመልክቶ አስፈላጊውን መመሪያ
እንዲሰጥና ቅድስት ቤተክርስቲያናችን ሰላምና አንድነት የሰፈነባት፤ በተሟላ ሥልት፤ አቅድና፤ ፕሮግራም
የምትንቀሳቀስ፤ በቅልጥፍና፤ በግልጽነትና በአስተማማኝ ቁጥጥር የምትሠራ፤ ስብከቷና ትምሕርቷ ለዓለም ሕዝብ
ሁሉ የሚዳረስ፤ የማትደፈር፤ ራሷን የቻለች፤ ምእመኖቿም በእምነታቸው የጸኑ የብዙ ሐገሮች ዜጎች እንዲሆኑ
እንዲያደርግ የሁልጊዜም ጸሎታችን ነው።
ቅዱስ ሲኖዶሱ፤ በመንፈስ ቅዱስ መሪነት፤ ባሁኑ ጊዜ በቤተክርስቲያናችን ላይ የተጋረጡትን ከባድ ችግሮች
በሚገባ እንዲወጣ ለቸሩ የኢትዮጵያ አምላክ ተንበርክከን እንጸልያለን። አሜን።
እጅግ ከፍ ካለ የአክብሮት ሰላምታ ጋር፤
ኢዮኤል ነጋ
የማሕበሩ ዋና ጸሐፊ።
ቅሌት
ሰሞኑን “ትኩረት” በሚል ርዕስ ዉስጥ የተጻፈ በራሪ ዎረቀት አንብበናል ። ቀደም ሲል “ “ደዎል” በሚል ርዕስ
ይቀርብ ከነበረዉ ጽሁፍ ጋር ተመሳሳይ ሆኖ አግኝተነዋል።
ስለ ቤተ ክርስቲያን ችግር “ትኩረት” ልትጠቁመን ሞክራ አልተሳካላትም።
ይልቁንም በዎያኔ አፈ ቀላጤዎችና ቦርድ ዉስጥ ባሉ ተወካዮቻቸዉ በኩል የተዋቀረዉ አዲሱ “ የቀድሞ የዕኛ
ሰዎች” ድርጅት ልሳን መሆኑን ተረድተናል።
ቦርድና ድርጂቱ በ”ትኩረት” አማካኝነት የቤተ ክርስቲያናችን ችግር በግለሰብና በጥቂት ሰዎች የተፈጠረ ነዉ ብለዉ
ልያሳምኑን ይሞክራሉ። በአባ ፓዉሎስ ቀሳዉስትና ዲያቆናት አማካይነት ሰፊ ቅስቀሳ እያደረጉ ነዉ፡ ለማዉገዝም
እየቃጣቸዉ ነዉ።
ከዚህም አልፎ ይህ የዎያኔና የአባ ፓዉሎስ ቡድን በከተማዉ ዉስጥ የታዎቁ የኮሚኒቲ መሪዎችን በማሳመንና
በሚቀጥለው ምርጫ የቦርድ አባል ሆነው እንዲመረጡ ቃል በመግባት የዚህ እኩይ ሃሳብ ተባባሪ አድርገዋቸዋል።
በተደረሰዉ ስምምነት መሰረት እነዚህ ግለሰቦች በከተማችን ዉስጥ በሚገኙት ሕቡዕ የማህበራዊና የፖለቲካ ፎረሞች
ላይ ዛሬ “ትኩረት” የሚያሰራጨዉን ሃሳብ አቅርበዉ ተሰብሳቢዉን ለማሳመን እየታገሉ መሰንበታቸዉ የአደባባይ
ሚስጢር ነዉ።
ከዚህም አልፈዉ ጁን ላይ በተደረገዉ አጠቃላይ የቤተ ክርስቲያን ጉባዒ ላይ ይሄንኑ ሃስብ እነዚሁ የኮሚኒቲዉ ግለ
ሰቦች አቅርበዉና ችግሩን በሽምግልና መልክ የሚያይ ኮሚቴ ለማስመረጥ መሞከራቸዉ አይዘነጋም።
ሕዝቡ መገንዘብ ያለበት ዎያኔ በተለያየ መልክና ይዘት ሊያጠፋን የሸረበዉን ተንኮል ነዉ። ስለ መሠረታዊ ችግራችን
ከዚህ በፊት ቤተ ክርስቲያናችንን ከቀበሌ የፍርድ ሸንጎ ወደ ተቀደሰ ደብር ለመለወጥ የተደረገ ጉዞ በሚል ርዕስ ስር
የተጻፈዉን እንድታነቡት እንጋብዛለን
የኽዉም በ “ብሎጉ” መጨረሻ ገጽ ላይ “Older posts” የሚለውን ስትጫኑ ክምታገኟቸዉ ጽሁፎች አንዱ ነው።
ቸር ወሬ ያሰማን!!!!!.

Wednesday, October 14, 2009

የቤተ ክርስቲያናችን ችግሮች በአስተዳደር ቦርዱ እይታ፡
የተመረጣችሁት፦
ተበላሽቶ የነበረዉን የቀድሞ አስተዳደር ለማስተካከል ነበር፡ በማስተካከል ፋንታ እያበላሻችሁ ነዉ
አይደል?
ዛሪ ያን አደራ ረስታችሁ ከቀድሞ የእኛ ሰዎች ከምትሏቸዉ ጋር እየተባበራችሁ በዱሮው አመራር
ያለ ምንም ለዉጥ እየሰራችሁ ነው አይደል?
ማህበረ ቅዱሳን መለካት የማይችል ፍዳ ላይ ጥሎን አሁንም የቢተ ክርስቲያን አባል ልታደርጉ
እየታገላችሁ ነው አይደል?
ይህንንም ባሳተማችሁት የቀን መቁጠሪ አና በይፋ ባፋአችሁም ገልጣችኋል አይደል?
የማህበረ ቅዱሳን አባል እና የ አባ ፓዉሎስ ተጠሪ ቀሳዉስት ቀጥራችሁ ህዝቡን እያስበጠበጣችሁ
ነው አይደል?
ይኅዉ ተጠሪ ካህን በጾም ዎቅት ብር ተቀብሎ ሲያጋባ ዝም አላችሁ አይደል?
ሕዝቡን ሲያዉኩ በመቅደስ ቆመዉ ሲሳደቡ እና ስለማህበረ ቅዱሳን ድርጅት በትምህርት መልክ
ሲያስተላልፉ ሰምታችሁ እንዳልሰማ ሆናችሁ አይደል?
የማህበረ ቅዱሳን አባል ለትምህርት ጋብዛችሁ አስመጣችሁ አይደል?
እነዚሁ ቀሳውስት ሕዝቡ ገንዘብ እንዳያዋጣ ሲቀሰቅሱ ዝም አላችሁ አይደል?
“ሕዝብ ለቢተ ክርስቲያን ገንዘብ እንዲሰጥ ለማስተማር መንፈስ ቅዱስ አላሳሰበንም” ብለዉ
በጉባኤ ላይ ስናገሩ ሰምታችሁ ምን አደረጋችሁ?
የማህበረ ቅዱሳን ቄሶቻችሁ እንግዳ ቄስ ላይ የስም ማጥፋት ዘመቻ ዎረቀት ሲበትኑ ምን
አደረጋችሁ? ዚም ብላችሁ አያችሁ አይደል?
የአባ ፓዉሎስና የማህበረ ቅዱሳን ቄሶች አድማ መትተዉ መቅደስ ዉስጥ ተደብቀዉ ሲዉሉ ዝም
አላችሁ አይደል?
ቄሶቹም እናንተም ቂም ይዞ ያለንስሃ መቀደስም መጸለይም ይቻላል ብላችሁ ታምናላችሁ
አይደል?
ማህበረ ቅዱሳን አገልግሎት የሚሰጡትን የነሱ ያልሆኑ አባላት ሰድበዉ ሲያባርሩ አይታችሁ ዝም
አላችሁ አይደል?
የሂሳብ አያያዝና የአስተዳደር ሥራት ይለዎጥ ቢባል አሻፈረን አላችሁ አይደል?
ግለጽ አሰራርን አትዎዱም አትቀበሉም አይደል?
ገቢዉን እንደፈለጋችሁ ማዉጣት እንጅ ባጀት አዉጥታችሁ በባጀት መስራትን አትዎዱም
አይደል?
ቤት ክርስቲያኑን እየጎዱ ያሉትን ቀሳዉስት ገንዘብ ባይኖርም ተበድራችሁ ደመዎዝ መክፈል
ታስባላችሁ አይደል?
ከሳሾች ጋር አብራችሁ መዶለታችሁን አትክዱም አይደል?
እነሱ ከዉጭ እናንተ ከዉስጥ ሆናችሁ ቤተ ክርስቲያኑን ለማዉደም እያሰባችሁ አይደል?
ካስዎጡኝ ዎይም እንደገና ካልመረጡኝ ይህን ቤተ ክርስቲያን አዎድመዋለሁ የሚል የቦርድ አባል
እንዳለ ታዉቃላችሁ አይደል?
መጠነ ሰፊ የሆነዉን የቤተ ክርስቲያኑን ችግር ከ መዕመኑ ጋር ስብሰባ ጠርታችሁ መላ መፈለጉን
አትፈልጉም አይደል?
ተቀዳሚ ዓላማችሁ እንደገና ካልተመረጣችሁ ይሄ ቤተ ክርስቲያን የሚደክምበትን እና
የሚዎድቅበትን መንገድ እያዘጋጃችሁ አይደል?
እንደገና በተደጋጋሚ ተመርጣችሁ የዱሮ ግብራችሁን (ብዝበዛችሁን) ለመቀጠል በምታደርጉት
ዘመቻ ይህን ቤተ ክርስቲያን ያለኛ በቀር ማስተዳደር የፍሚችል የለም በሚል ሽፍን ቅስቀሳ በ
አፈ ቀላጤያችሁ እያስዎራችሁ ነዉ አይደል?
ምርጫዉ ካልተሳካላችሁ የእኛ ዎገኖች የምትሏቸዉን ሰዎች አዘጋጅታችሁ ለማስመረጥ ቅስቀሳ
ጀምራችኋል አይደል?
ደብራችን ላይ ይህን ሁሉ ደባ እየፈጸማችሁ ለምን ተብላችሁ ስትጠየቁ ስማችሁ ስለተጠቀሰ
እንደ እብድ አደረጋችሁ ( እዉነቱን ሲነግሩት እንደ ኮለኮሉት ያህል ይስቃል) እንደሚባለዉ
እዉነቱ ሲዎጣባችሁ አሳበዳችሁ አይደል?
የዚህ ሁሉ ጥያቄ መልሱ አዎን ነዉ፡
ማሳሰቢያ፦
በዚሕ አትም አባልና ተቆርቋሪ የሆናችሁ የሚካኤል ዎዳጆች በሙሉ ከላይ የተጠቀሱትን
መንደርደሪያ አድርጋችሁ ቤተ ክርስቲያናችን አደጋ ላይ መሆኑን ተረድታችሁ የሚጠነሰሰዉን
የሃሰት ተንኮል እንድትረዱ ነዉ፡
ለምሳሌ ያህል የቦርዱ ሊቀ መንበር የሚያሰራጨዉ የሃሰት ፕሮፓጋንዳ የማይፈለጉ ቄሶች
የማይዎጡት ከሳሾቻችን ጋር እንዳይተባበሩ ነው የሚል አሳሳች ሃሳብ የሚያሰራጭ መሆኑን
ነግሯችኋል፡
የህግ ሰርቲፊኬት እንዳለዉ ሊያሳየን ይሆን?
ዎይስ ጠበቃ አነጋግሮ ይሆን?፡ ከከሳሾችህ ጋር ይተበበራል ያለዉ?
ይህ አዎናባጅ ግለሰብ ቤተ ክርስቲያኑን ክመበዝበዝ አልፎ ተርፎ የማን አለብኝ ስራ አየሰራ
መሆኑን መዘንጋት የለብንም።
ዉድ ሊቀ መንበራችንና ግብረ አበሮቹ ህዝቡ እንዳልተደሰተ በየቀኑ የሚደርሳቸዉን እሮሮ
እየሰሙ የመረጣቸዉን ሕዝብ በማገልገል ፋንታ የተለየ አጀንዳ እንዳላቸው ያሳያል፡
የቄሱን አቀጣጠር ባለፈው እትማችን ገልጸናል።
እኝሁ ቄስ ህዝቡን እንዲካፋፈሉ የተቀጠሩበትን ስራ እየሰሩ መሆኑን ለማንም ግልጽ ነዉ፡
እኝሁ ቄስ ”የአስተዳደር ቦርዶች እግሬ ላይ ዎድቀው ተማጥነዉኝ ነው እንጅ እኔ ለማገልገላል
ፍላጎት አልነበረኝም” ማለትም ማንነቴን አዉቀዉ ነው የቀጠሩኝ ማለታቸዉን ብዙ ሰው
ስምቶታል፡
ዪሄዉ ለቀ መንበር የማን አለብኝ ስራ እየሰራ መሆኑ ግለጽ ስለሆነ ከ ቦርዱ እንዲባረር መጠይቅ
የሁላችንም መብት መሆኑን አንዘንጋ።
ይሄው ሊቀ መንበር ካሁን ቀደም ካባረሩኝ፡”ይሄን ቤተ ክርስቲአን አዉድሜው ነው የምዎጣዉ
ማለቱን መዘንጋት የለብንም።
በሰላም ክዎጣም በኋላ የዎያኔ መንግስት ተጣሪ የሆነው ጓደኛዉ የኢትየፕያ መንግስት ደጋፊህ
ስለሆነ ተመለስ ብሎሃል ብሎ እንደመለሰዉ ለማንም ግልጽ ነዉ.
ከዎያኔ መንግስት ነጻ መሆናችንን ለማሳየት የምንችለው ይሄን ግለሰብ እስከጓደኛዉ በሰላም
ስናሰናብት ብቻ መሆኑን እዎቁ።
በሚቀጥለዉ እትም መልካም ዎሬ እንዲያሰማን እንጸልይ።

Tuesday, September 29, 2009

እግዜኦ!!! አግዚኦ!!!
አቡነ ቆስጦስን ዎደኛ ቤት ክርስቲያን አስመጥቶ ቤት ክርስቲያኑን ለማስረከብ ሙከራ ሲደረግ
ሆዳቸው አልጨክን ያላቸዉ የቤት ክርስቲያኑ ዎዳጆች እንዳከሸፉት ብዙዎቻችን እናስታዉሳለን።
የዳላስ ቤተ ክርስቲያንም አልቀበላቸዉ ሲል በ ዋሽንግቶን ዲሲ አካባቢ ሆነው ያአባ ፓዉሎስን
ትዕዛዝ በስራ ላይ ሲያዉሉ መክረማቸዉ የታዎቀ ነው። በዚህ ዎቅት እኝሁን አቡን የተቀበሉት የ
ድ.ሲ ቤት ክርስቲያን መሪ ( በነገራችን ላይ ዶክቶሩ የ ሊቀ መንበራችን የገል ጓደኛ ) የዎያኔ
መንግስት ፕሬዚደንት ሊያደርጋቸዉ ነዉ የሚል ዎሬ በመላው አሜሪካ ያስነፍሱ የነበሩት ዶክተር
ናቸዉ።
እንዳጋጣሚ በዚሁ ዎቅት የደንቨር ቤት ክርስቲያን ደግሞ ካህን ይፈልግ ነበር። እኝህ በአሁኑ ጊዜ
እኛ ጋ የተጠጉትና መስቀልን እግዚአብሄር የተሰቀለበት ማስታዎሻ ከመሆኑ ይለቅ አንደ አንድ
የማንም የስራ መቀጠሪያ ድፕሎማ ገትረው ዲፕሎማየ ነው የትም ሄጀ መቀጠሪያየ ነው የሚሉት
ቄስ እንዲቀጠሩ ይጠቆማሉ ። ዪህ ጥያቄ አዲስ አበባ በደረሰ ጊዜ የለምንም ማጣሪያ ባስቸኩዋይ
ያባ ፓዉሎስን እቅድ ለሟሟላት እንዲመች ዎደ አሜሪካን ይላካሉ።
የመቅጠር ፍላጎት የነበረዉ ቤተ ክርስቲያን ሚስጥሩን ስለደረሰበት ሃሳቡን ለዉጦ ሌላ ቄስ
ሲቀጥር እኝሁ ጉደኛው የእኛ ቄስ ከአቡነ ቆፕስጦስ ጋር በ ዋሽንግቶን ዲሲ ቤት ክርስቲያን
ተዳብለው ሲበጠብጡ ኖሩ።
አቡነ ቆስጦስ የዳላስን ቤተ ክርስቲያን መረከብ ህልማቸዉ ስለከሸፈ መዕመናኑን ሊበትንና
ሊከፋፍል ይችላል ብለው ያመኑበትን እኝህን ቄስ ከዎያኔ መንግስት ተስፈኛ ፕሬዚዳንት ጋር
በመሆን በቤተ ክርስቲያናችን የቦርድ ሊቀመንበር አማካኝነት አስቀጠሩ።
የሄዉም ሊቀመንበራችን እኝህን ሰው ካስቀጠረ ዶክተሩ ፕሬዚዳንት ሲሆኑ አዲስ አበባ ሄዶ
የመንግስት ስራ ሊሰጠው ቃል እንደተገባለት ይህን ጉድ ያዎጣዉና ቤት ክርስቲያናችንን ከሽያጭ
ያዳነው ቡድን ገልጾታል።
እኝሁ ቄስ የተማመኑበትን ጋሻ ለማሳየት በየጊዝዉ በሚያሳዩት ተግባር እየገለጹ መሆኑ ለማንም
ድብቅ አይደለም።
ሁለት ጊዜ በተደረገዉ አጠቃላይ ጉባዔ ላይ ተነስተዉ መስቀላቸዉን ክፍ አድርገዉ ይዘዉ
እንጠቅሳለን (ይህን መስቀል እስከያዝኩ ድረስ የትም ሄጀ መስራት እችላለሁ) ብለዉ ደግመዉ
ደጋግመዉ ማስጠንቀቂያ ይሁን ዛቻ እንደነገሩን ሁላችንም ልብ ብለናል።
ይሄም የሚያሳየው የጨበጡት መስቀል ማዎናበጃ እንጅ እዉነት የክህነት ትምህርት አለመሆኑን
ነዉ። ዋና አላማቸዉ ህዝቡን ለመበታተን እንጅ እዉነትም የዕየሱስን ትምህርት ለማስተማር
እንዳልመጡ እየገለጹ መሆኑን ለዕናንተ ለመዕመናኑ እንድትረዱት ማድረግ አስፈላጊ
አይመስለንም የገዛ ስራቸዉ እየገለጠዉ ነዉ።
ፍትኅ ነገስት አንቀጽ 6 ቁጥር 210፦
ቄስ የእግዚአብሄር ሹም እንደመሆኑ ነዉር የሌለበት ይሆን ዘንድ ይገባዋልና፡ በራሱ ፍቃድ
የሚኖር አይሁን፡ ቂመኛ አብዝቶ የሚጠጣ ለመማታት እጁን የማያፈጥን አይሁን ያልታዘዘ
ትርፉን የሚዎድ አይሁን፡ እንግዳ መቀበልን የሚዎድ በጎ ስራን የሚዎድ ንጹህ ድንቀ ቸር የሆነ
ዎዘተ…
አንቀጽ 6 ቁጥር 224፦
የሃጢአተኛዉን ንስሃ የማይቀበል ዎይም በነገር ሠሪነት ሃሰትን በመመስከር የሚታበይ ሕግን
አዉቆ የማይሰራበት ክፉ ስራንም የሚያዘዎትር በጎ አለመስራትን የዎደደ ዎይም አለቃዉ
ሳይፈቅድለት ዎደ ንጉሥ የሚሄድ ቄስ ይሻር።
አንቀጽ 6 ቁጥር 234፦
በነገረ ሥራ አይመስክሩ ሰዉንም ለማክሰስ ዎደ ንⷝስ አይሂዱ፡ ሓሜተኞች አይሁኑ። ለመዕመናን
ክፋትን አይዉደዱ። ከነርሱ ዎገን ይህን ያደረገ ከሹመቱ ይሻር ዎዘተ…….
ቤተ ክርስቲያናችን ይህን መጽኅፍ የምትቀበል ከሆነ የእኛ ሁለቱ ቄሶች መቅደስ ዉስጥ ገብተዉ
መቀደስ ይችላሉ ዎይ?
ዎይስ የአስተዳደሩን ሥራዓት እንዳጣመምነው ዎደ መቅደሱም ችግሩን አስገብተን እያፌዝን
ነው።
ዋና ደጋፊአያቸዉ ያሁኑ ልቀ መምበር የመዕመናኑን መብት እየረገጠ የዎደፊት አገር ዉስጥ ገብቶ
ሊሾም መንገዱን እየጠረገ መሆኑን በግብር እያሳየ ነዉ።
ደግመን ደጋግመን ንስሃ እንዲገባ መለመናችንን አሁንም አንተዉም።
እሱ ግን ከቀን ዎደ ቀን በሚያሳየዉ ተግባር እየባሰበት መምጣቱንና አልፎ ተርፎ ከ ከሳሾቻችን
ገር በጥቅም እየተዋቀረ መሆኑን አጥብቀን መቆጣጠር ይኖርብናል።
በሚቀጥለዉ እትም ከከሳሾች ጋር የሚያደርገዉን ግኑኝነት እናበስራለን።

Friday, September 25, 2009

የሽማግሌን ኮሚቴ በአዲስ መልክ ለማዋቀር ጅምሩ ቀጥሏል!!!!!
የአስተዳደር ቦርድ የአማካሪ ኮሚቴ ብሎ ይጠራቸዋል፡ ህዝቡ ደግሞ የሽማግሌዎች ኮሚቴ ብሎ
ይላቸዋል። እንደት እንደተሰባሰቡ አልፈዉ ተርፈዉ ስማቸዉ ተሻሽሎ የቤተ ክርስቲያን ቋሚ
ኮሚቴ ለመሆን መብቃታቸዉን ሁላችሁም የምታዉቁት ታሪክ ነው።
ይህ በቋሚነት አገልግሎት መስጠት ላይ ያለው ኮሚቴ ክተቋቋመ ጊዜ ጀምሮ ያስገኘዉ ተጨባጭ
የስራ ዉጤት ምን ይሆን? የቤተ ክርስቲያናችንን ችግር ለመፍታት በተደረገዉ ጥረት ዚሁ
ኮሚቴ ድርሻ ምን ነበር?
ዎይስ ካሉን ችግሮች መሃል አንድ ዋናዉ ይሆን?
ለነዚህ ጥያቄዎችና እነማን እንደሆኑ እስከ ሽፍን አላማቸው ጋር ትንታኔ በዎቅቱ ዎደፊት
እናቀርባለን።
ለዛሬ ልንገልጽላችሁ የምንመኘዉ በማህበረ ቅዱሳንና በአባ ጳዉሎስ ተዎካዮች አማካኝነት
ተመርጦ በሽምግልና ስም ቤተ ክርስቲያናችን ዉስጥ መንቀሳቀስ ስለጀመረው ቡድን ይሆናል።
ይህ ቡድን ከአባ ፓዉሎስ ልዩ መልክተኛ ከ ንቡረእድ ጋር በማህበረ ቅዱሳን አማካኝነት
ተገናኝቶ በሽምግለና ስም እንዲቀሳቀስ ከተመረጠበት (August 18 2009) ዓ. ም ጀምሮ
እኛ እስከምናዉቀዉ ድረስ አራት ስብሰባዎች ሲያደርግ ሁለትን ያደረገዉ ከአስተደር ቦርዱ ጋር
ነው፡ ከላይ የተጠቀሱት ስብባዎች ሂደት እንደሚጠቁመዉ ዎደፊት ቋሚ የሽማግሌዎች ኮሚቴ
አባላት ለመሆን እየታጩ መሆኑን ይጠቁማል።
ከ ሰላሣ በላይ የሆን ማህበርተኞች የአስተዳደር ቦርዱን ለማነጋገር እንፈልጋለን ብለን በደብዳቤ
ብንጠይቅ ጥያቂአችንን ላለመቀበል የተለያየ ምክንያት በመፍጠር እንዲጓተት ተደርጓል፡
ሕዝቡን ቀርቦ ማነጋገር ያስፈራቸዉ ለምን የሆን?
ከላይ የተጠቀሰው የሽማግሌ ቡድን ግን የለፈው ቅዳሜ ማታ በስልክ ስብሰባ ጠይቀው ሰኞ ምሽት
ከቦርዱ ጋር መሰብሰባቸዉን እናዉቃለን።
በዚህ የአሰራር ልምድ ስለ ቦርዱ ለመገንዘብ የቻልነዉ ፦
የቤተ ክርስቲያኑ መዕመናን የመረጠዉ ቦርድ የተመረጠበትን አላማ ስቶ ለጥቅም ብቻ
እንደሚተዳደርና የመዕመናኑን ጉዳይ እና እሮሮ አልሰማም አሻፈረኝ እንደፈለጋቸዉ
ይሰደቡ!!ይሰዳደቡ!!! የት ይደርሳሉ?
የሚል አቋም እንዳለው ነው፡
የመረጠዉ መዕመናን ጋር ከሚገናኝ ይልቅ አባ ፓዉሎስ ከላኩት መለክተኛ ጋር መገናኘቱን
ለምን መረጠ ይሆን?
በኛ አስተሳሰብ ቦርዱ ከማህበረ ቅዱሳንና ካባ ፓዉሎስ በሚሰጠዉ መመሪያ እንደሚንቀሳቀስ ይፋ
ማዉጣቱን እያረጋገጠ መሁኑን ያስረዳናል።
እግዜር ቸር ዎሬ የምንሰማበትን ቀን ያቅርብለን።
በሚቀጥለው እትም ስለ ቀሳውስቱና በምን ዘዴ እንተቀጠሩልንና መስቀልን የጌታ እየሱስ ክርስቶስ
ምልክት መሆኑ ቀርቶ ማስፈራሪያ መደረጉን እንገልጽላችኋለን።

Wednesday, September 23, 2009

የእዉነት ያለህ
ቤተ ክርስቲያናችን ላይ የተሰነዘረው ጥቃት የተቀነባበረው በኢሃድግ መንግስት
ነው፡
በደካማ ጎናችን ገብቶ እያጠቃንም ነው፡ ይሕም ሊሆን የቻለው አስተዳደሩ ስራት
ያለምንም ማዕቀብና ቁጥጥር የተዋቀረ በመሆኑ ነው፡ በዚህም ምክንያት ከዉስጥና
ክዉጭ የተሞከረውን አደጋ መቋቋም አቅቶት ሲንገዳገድ ይታያል።
ባለፉት 19 አመታት የተከትልነው አስተዳደራዊ አስራር ተንዶ ለፍርድ ሸንጎ
ዳርጎናል።
ዎደፊት ለመጓዝና ይህን ብልሹ አስተዳደር ለመለዎጥ መፍትሄው፡ ግልጥ! ያለ
የአስዳደር (ትራንስፓረንሲ) ያለው አሰራር መዘርጋት ነው።
የህም ግልጥ አሰራር በሂሳብ መዝገብ አያያዛችን መጀመር አለበት የሚል ሃሳብና
ዕቅዱ ላስተዳደር ቦርዱ ቀረበ። ቦርዱ ግን ይህ የአሰራር ዘዴ ከቀረበለት ቀን ጀምሮ
ይህን እቅድ መቃዎሙን ተቀዳሚ ስራው አደረገ። ይባስ ብሎም ሃሳቡን ያቀረቡ
አባላትን ስም እየጠሩ ስራ አላሰራ አሉን በማለት የስም ማጥፋት ዘመቻን ስራየ
ብለው ተያያዙ። ለምን?
በ2007 ዓ.ም በበጎ አድራጎት ኮሚቲ አማካኝነት ዎጭ የሆነውንና እስከ ዛሪ ድረስ
ይህ ኮሚቲ ደረሰኝ ሊያቀርብበት ያልቻለውን ሰነዶች በ2008 ዓ.ም ላይ
ለመዕመናኑ መበተኑ ይታዎሳል። በዚህ ሰነድ ላይ ስማቸዉ የተዘረዘረው ግል ሰቦች
በሙሉ የዎሰዱትን ገንዘብ አባከኑት ተብሎ ክስ አልቀረበም? ይልቁንም የሰነዱ
መሰራጨት ዋና አላማ የነበረው ማህበረ ቅዱሳን በስሩ የሚተዳደሩ ቤተ
ክርስቲያናትና የራሱን የግል ስራ ለማስፈጸም በአንድ አመት ውስጥ ብቻ ስንት ብር
አንደዎሰደ ለማሳየት የተደረገ ሙከራ ነበር። ዓላማዉ በብዙ ዉጣ ዉረድ ግቡን
ሊመታ ችሏል፡ በዓንጻሩም የህ ሰነድ ዛሬ ይፋ ሆኖ ለመጣዉ ችግር ምክንያት
ሆኗል።
የአስተዳደር ቦርዱ በየሶስት ዓመቱ በሂሳብ አጣሪ (CPA) አስመርምሮ ለመዕመናኑ
የሚያሳዉቀዉን የሂሳብ ዝርዝር (ኦዲት) ማቅረብ ያቃተዉ በዚህ ለሕዝብ
በተበተንዉ ሰነድ ምክንያት ነው።
የኦዲተሩ አቀጣጠር ከመተዳደሪያ ደንቡ ዉጭ ያለምንም ጨረታ በትዉዉቅ መጥቶ
የተቀጠረ ሂሳብ ተቆጣጣሪ ነዉ። ይሄው ተቆጣጣሪ ቀደም ሲል ለቤተ ክርስቲያኑ
ተመሳሳይ አገልግሎት መስጠቱ አይዘነጋም። የሂሳብን መዝገቡ እንደምንፈልገው
በማቀነባበር አቅርብልን (COOK THE BOOK) ማለትም ዋሽልን ተብሎ ሴጠየቅ?
ሳያመነታ የደንበኞቹን ፍላጎት እንጅ የጠራ የሂሳብ የመቆጣጠር ስራ የሰራ
እይደለም።
ይኄዉ ግለስብ ባለፈዉ የአስተዳደር ቦርድ የዎጭ ሰነዶችን ደምረህ በምታገኘዉ
ቅምር ሂሳቡ እንደተዎራረደ አድርገህ አቅርብልን ብለው ቀጥረዉ እንደተጠየቀዉ
ሰርቶ በማቅረብ ኦዲት በ (C P A) ተደረገ ምንም የጎደለ ሂሳብ የለም ተብሎ
በጭብጨባ ሪፖርቱን መዕመናኑ እንዲቀበል ተደርጎ በሽፍንፍን መታለፉን
ሁላችንም እናውቃለን።
የዛሬዉም ቦርድ ይህንኑ አሰራር ለመድገም ቀና ደፋ ሲል ተደርሶበት፡ የለም ይህ
አሰራር ዖዲት ሳይሆን የዎጭ አጠቃላይ ድምር ዉጤት ነው ሲባል ልስራው
መጓተት ምክንያት ሆነ።
ዉድ መዕመናን አንድ ሰነድ ይህን ያህል የሰዉ ዓይን ክገለጸ ዎደ ኋላ የ አስር
ዓመት ሂሳብ ዖዲት ይደረግ ቢባል ዉጤቱ ምን የሚሆን ይመስላችኋል?
እኛ አባላቱ ይህን የመጠየቅ መብት የለንም ይሆን? ዎይስ ጥቅማቸዉ የተነካ
የዘራፊዎች ቡድን እንደሚያሰራጩት ዎሬ ይህን “ የፍሚጠይቁና የሚጽፉ የኛ
ሰዎች አይደሉም “ እየተባለ የኛ ሰዎች አይናቸዉን የከፈቱ አይደሉም
“ያደረግነውን ብናደርጋቸዉ የኛ የሆኑ አይቃዎሙንም” ገንዘባችንና አቅማችንን
አዋጥተን የጀመርነውን ቤት ክርስቲያን መበዝበዝ ቀርቶ መሸጥም እንችላለን እያሉ
ስለሚፎክሩ ከበይ ክፍል ያልሆነ ሁሉ የነሱ ሰዉ አይደለም ለማለት ይሆን?
እንድታዉቁልን የምንፈልገው እኛ አንዳዶቻችን ይሄ ዲርጊት በዛ ይቅር ሳያዋርደን
እናቁመዉና ዎደ መልካም ተግባር እንመለስ የምንል ነን ይሄንንም ያደረግነው
እናንተን ዘመዶቻችንና ጓደኞቻችን ትለቅ የሃፍረት ካባ እንዳትጎናጸፉ ነዉ።
በዚሁ ማስታዎሻ አማካይነት ግለጥ (ትራንስፓረንሲ) አሰራርን አብዛኛቹ የቦርድ
አስተዳደር አባላት የቀድሞዎቹም ሆኑ አሁን ያሉትና ደጋፊዎቻቸዉ ሽንጣቸዉን
ገትረው እየተቃዎሙ መሆናቸዉን እንድታዉቁ ለናንተ ለመዕመናኑ ማስረዳቱ ተገቢ
ነው፡ ይህም የሚሆንበት ምክንያት እንደ ድሮው እንደፈለግን እናደርጋለን እንጅ
ማንም እንዲቆጣጠረን አንፈልግም፡ አንዳንድ እነዙህ የኛን ሰዎች የሚነካ ጥያቄ
ሲነሳ አፍንጫ ሲነካ ዓይን ያለቅሳል እንደተባለው እኛዉ በኛዉ ተጠራርተን
እናፈርሰዋለን እንጅ ከ ዱሮው አሰራር አንዎጣም፡ ዘላለም እንደበዘበዝን አንኖራለን
እንደሚሉ ነዉ።
በሚቀጥለው እስትንገናኝ ደህና ሁኑልን።
ዎስብሃት ለዓምላክ።

Thursday, September 10, 2009

አልሞት ባይ ትጋዳይ።

የ ቦርድ አባሎቻችን በየቀኑ የምናስተላልፈዉን ጥያቄ በስራ ላይ ላለማዋል የሚያደርጉትን ጥረት በይፋ እያስታዎቁን መሆኑን ለናንተ ለምዕመናኑ ለንገልጽ እንፈልጋለን።
ጧትና ማታ ቤተ ክርስቲያናችንን አይናችን እያየ አብረው ካንዳንድ የቦርድ አባላት ጋር ሆነው የዘረፉንን እና በቤተክርስቲያናችን ዉስጥ እያሞለጩ የሚሰድቡንን (ፓራሳይት) አስዎግዱልን እያልናቸዉ እንዲያዉም ማን አለብን ብለው እነዚሁ ዘራፊዎች ዎር ተለዉጦ ሌላ ዎር ሲጀመር
የምንከፍተዉን የዎር መቁጠሪያ በገለጥን ቁጥር እያየን ሆዳችን እንዲቆስል፡ሊለጠፍ የሚገባዉ ስንት የቤት ክርስቲያን ምስል እያለ የማህበረ ቅዱሳንን የዘማሪ ምስል ለጥፈው ለመዕመናኑ መሸጣችዉን ልብ ብለን አይተናል።

ይሕንንም የቅሌት ስራ የፈጸመችው የቦርድ አባል ባስቸኩዋይ ህዝቡን ሰብስባ ይቅርታ በፍመጠየቅ የቸረቸረችዉን የቀን መቁጠሪያ ሰብስባ ሌላ ቤተ ክርስቲያኑን የሚዎክል የቀን መቁጠሪያ አሳትማ ለከፈሉት ሁሉ እንድታድል እንጠይቃለን።
ተሳዳቢ የዎያኔ ቄስ ከማስመጣትዋም በላይ ባለፈው ጊዜ እየተነገራት የማህበረ ቅዱሳን ዋና ተዎካይ የሆነ የስድስት ዎር ቄስ ቤተ ክርስቲያናችን ዉስጥ መጥቶ እንዲያስተምር አድርጋለች፡

በትላንትናዉም የቤተ ክርስቲያናችን ክስ ለከሳሾቻችን የተፈረደላቸዉን ፊርድ በሚመለከት የአባላት ስም ዝርዝር እንዲሰጥ ስለተደረገ መደሰቷን ደርሰንበታል።
ይህችም ዎይዘሮ ከበላይ ሆኖ የቦርድ አባላትን ዎደ ሸር መንገድ እንዲጓዙ የሚመራ ባለቤቷ ጋር
የጠነሰሱት መሆኑን በግለጽ ተረድተናል፡

ተጨባጭ የሆኑ ማስረጃዎችንም ከያዝነው ዎር አጋማሽ በኋላ በምናቀርባቸዉ አትሞችና የድምጽ ሲዲዎች እናቀርብላችኋለን፡
የሄ ሁሉ የቦርድ አባሎች ጥፋታቸዉን አዉቀው ንስሃ ክገቡ ማጋለጣችንን እናቆማለን ብለናል እስክዚያ ድረስ ግን አሁንም የቦርድ አባላት ሁሉ ዎደ መልካም ተግባር እንዲመለሱ እንጸልይላቸው!!!!!!።

Wednesday, September 9, 2009

መልካም ዎሬ ላንባቢዎቻችን፡
ቤተ ክርስቲያናችንን ከ (ፓራሳይት) እና ዉስጣችን ሆነው ሊሸጡን ከሚያስማሙን ከሃዲዎች ነጻ ለማድረግ የተያያዘው እሳት እየተቀጣጠለ ነው።
ዛሬ ደግሞ አዲስ ብሎግ “ ( ብሎግ) ምን ማለት እንደሆነ ለማያዉቁ መሃይማን ለዎደፊቱ እንተረጉምላችዋለን”
ማግኘታችንን ለናንተ ንጹህ ለሆናችሁ የ ቤተክርስቲያን አማኞች እናቀርባለን።
ብዙ ተከታታይም እንደሚኖረው ተረድተናል በጥሞና አንብቡት እንላለን
ብዙም ትምህርት እንደምናገኝበት አንጠራጠርም።


http://nenewe.blogspot.com/

በሰላም ቤተ ክርስቲያናችን አሸናፊ ይሆንልን ዘንድ መጸለያችንን አናቆምም፡

Sunday, September 6, 2009

ዛሬ ከብረዳሞ ብሎግ ላይ ያገኘነዉን ዎሬ ለናንተ የማህበረ ቅዱሳን ደጋፊዎች “ እነ አቶ ዒዩአል እና መላው የቦርድ አባላት” አፍኖ ይዞ ማህበረ ቅዱሳንና ከሳሾቻችን ቤተ ክርስቲያናችንን ይፈንጩበት እንደፈለጉም ያድርጓችሁ እንዲያዉም ብትዎዱም ባትዎዱም ልንታረቅና ዎደ ድሮው ልንመልሳችሁ ነው ብለው በሚስጥር ሳይሆን ባደባባይ ጠላቶቻችን ጋር እየዶለቱ መሆኑን እንድታዉቁልን ስለምንፈልግ ይሀኑ ብሎግ ኮፒ አድርገን እናትማለን፡
ፈቃድም እንደማያስፈልገን ተረድተናል።
ከዚህ እትም ጋር የምንስማማዉ ፍሬ ነገር ቢኖር፡ እኛም የተፈለገው ጥያቄ ተፈጽሞ ባስቸኳይ እስራላይ ከዋለ በያዝነው መንገድ ጉዞዋችንን እንደምናቆም ቃል እንገባለን።
የብሎጉ አድራሻ የሚከተለው ነው

http://debredamo.blogspot.com/
ዉድ የዳላስ ቅዱስ ሚካኤል ምእመናን፡
ባለፈዉ እትማችን ላይ አስተያየታችሁን ስጡን ብለን መጠየቃችንን እያስታዎስን
እንዳሰብነዉም ባይሆን ጥቂቶቻችሁ ያደረግነዉን አዳንድ የቀለም ስህተት እና የግል ጥላቻ
ያደረብን መሆኑን ገልጻችሗል።
ለማእመናኑ ለመግለጽ የምንፈልገው
አንደኛ፡
የኮምፒተርም ይሁን የመጻፍ ልምምድ የለንም፡ የቤተክርስቲያናችን ሁኔታ በጣም
ስላሳሰበንና መንገዱም ስላላማረን በተቻለን መጠን ዎደ መልካም መንገድ እንዲመለስልንና
እንደዱሮአችን ለጸሎት ስንገናኝ ተሳስመን ተሳስቀን አብረን በልተን ጠጥተን እስከሚመጣዉ
ጊዘ ጤና ይስጥለን ተባብለን እንድንለያይ ነዉ።
ከዛሬ አራት አመት ጀምሮ የሆነዉን ሁላችሁም ታዉቁታላችሁ። ቤታችንን ሰብሮ ገብቶ
ያበጣበጠንን በግለጽ ዓይናችን እያየ የዘረፈንን (ፓራሳይት) ለማባረር አስበን ነው።
ስለዚህ የቆሳቁስ ስህተቶቻችንን ታገሱና እለፉን።
ሁለተኛ፡
ከአቶ እዩኤልም ሆነ ከለሎቹ ጠብም ትዉዉቅም የለንም። አቶ እዩኤልን የምናዉቀው
እቤቱ ቁማር ስንጫዎት ማደራችንን እና የብዙዎቻችን ቤት ማፍረሱን ነው፡ ዋናዉ
ሃሳባችን፡ ማህበረ ቅዱሳን የተባለ የሰይጣን ተላላኪ ለነፍሱም ሆነ ለስጋዉ ልክ እንደ ቁማር
ማጫዎቱ የማይጠቅመዉ መሆኑን እንዲረዳ እና እነሱን ትቶ ዎደ መልካም ተግባር እንዲመለስልን
በማሰብ ነው።
(እንደምናውቀው የቅዱስ ሚካኤል ወፍጮ ጊዜዉን ጠብቆ ጠላቶቹንና የሚበዘብዙትን
እንድሚፈጭ አንጠራጠርም፡ ጊዜውንም ስለዎሰደ ያልፋቸዋል ማለት አለመሆኑን ይረዱ)
መመለሳቸዉንም የምናዉቀዉ ባስቸኩዋይ ቦርድ የቤተክርስቲያኑን አባላት ሰብስቦ ጥር ሰላሳ
አንድ ቀን ያሳለፉትን አዋጅ በስራ ላይ እንድዉል ሲደረግ ነዉ።
የፈሰሰ ዎሃ ተመልሶ እንደማይታፈሥ ስለምናዉቅ፡ የሂሳቡን የኦዲት ዉጤት ለኛ ማቅረብ በቦርዱ
ላይ የባሰ ሃሜትና መሳለቂያ መሆን እንጅ ምንም ፋይዳ እንደማያተርፍ አሁን ያለው ቦርድ
እንዲያዉቁት እንፈልጋለን።
ይህም ምክንያት ሆኖ ጊዜ የሚያራዝምበት ጉዳይ አይታየንም፡
እስክ እዚህ ዎር መሃከል ድረስ አንድ ዉጤት ካላገኘን ግን ትግላችንን እንደምንቀጥልና ይኽን
መልእክትና ሌሎችንም የተጨበጡ ማስረጃዎች እያቅረብን በእትም ብቻ ሳይሆን በድምጽ ማንበብ
ለማይዎደው ምእመናን እንደምንበትን እወቁለን።
ምእመኑን እንዲያዎናብዱ የምትልክዋቸው ግብረ አበሮቻችሁ ተሰብስበው ቤተክርስቲያናችን
ሊዎሰድ ነዉ ሊከሰስ ነው እያሉ ሃሰት የሆነ ዎሬ ማዉራታቸዉንም እናዉቃለን፡ ሁለት አይነት
ጸጉር ያበቀለ አዛዉንት እንዴት ያልሆነ ዎሬ ያዎራል እያልን እንደነቃለን።
አሁን ላላችሁት ቦርድ አባላት የምናሳስበው ባስቸክዋይ ኦዲት አስደርጉ ብሎ የመከራቹሁ እና ኦ
ዲተር ያቀረበላችሁ ግለሰብ ሊያዋርዳችሁ እንጅ ሊጠቅማችሁ እንዳልሆነ ተገንዘቡ ማንም
እንደሆነ ከነታሪኩ ከዚህ ዎር ግማሽ በኃላ በምናደርገው እትምና ድምጽ እናዎጣለን፣
ልዩ መልእክት፡ ላቶ እዩኤልና አሁን ላላችሁት የቦርድ አባላት.፤
እኛ ካንተ ጋርና ከሞላ ቦርድ አባላት ጋ ምንም ጠብ እንደሌለን አስቀድመህ እዎቅልን የኛ ዋናው
ጠባችን ከማህበረ ቅዱሳን ጋር አብረህ የምትዶልትበት ምክንያት ነው። ለምሳሌ ያህል ባለፈው
ዎር ከከሳሾቻችን ጋር በድብቅ ተገናኝተህ የተስማማኸዉን ስምምነት ተነግሮናል እንዲያዉም ማን
አለብኝ ብለህ ጨለማ ለብሰህ የቤተክርስቲያን በር ከፍተህ አስገብተህ ዉጭ በር ላይ ቆመህ
ጥበቃ ማድረግህን በአይናችን አይተናል.፡
እንዲሁም በይፋ የቤተክርስቲያን ከሳሾች የገንዘብ መሰብሰቢያ ወረቀት እያዞሩ ሲያድሉና
ሲያሳድሉ እያየህ ዝም ማለትህ የሚያሳፍር ተግባር ነው። ይህ ድርጊት አንተ ላይ ብቻ ሳይሆን
በመላው ቦርድ ላይ እንደሚያርፍ ቦርድ አባል የሆናችሁ ተረዱ።
በተጨማሪም ከዕግዚአብሄር ጋ የተላኩልን የቅዱስ ሚካዒል ቄስ እና የቦርዱ ዋና ጸሃፊ ባሉበት
አገር እያቁዋረጡ የሚመጡት የዎያኔና ያባ ፓዉሎስ ተዎካይ በግለጽ ድቪድ እና ጥብቆ ሲሸጡ
ዝም ብለው ሲያዩ እንደነበረ ሰምተናል፡
ይህም ዋና ጸሃፊ አስቆምኩዋቸው ማለቱን ሰምተናል፣ሸጠው ሲጨርሱ ማስቆምና ዎዲያው እንዳየ
ፖሊስ ጠርቶ ማስነጠቅ ተግባሩ እንደነበረ የዘነጋው ይመስላል፡
ምዕመናን ሆይ እኛንና እንደናንተ ያለዉን የ ማህበረ ቅዱሳን ደጋፊ ያልሆነዉን ይሀዉ ጸሃፊ ይሄን
ስራ ሰንሰራ ቢያይ እንደሚያሳስረን አትጠራጠሩ፤
አንዱ የቦርድ አባል የሚያደርገው ሃጤአት ሁላችሁንም የቦርድ አባላት እንደሚያስዎቅስ
እንድታዉቁለን እንፈልጋለን።
እባካችሁ ለኛም ለነብሳችሁም፤ ማህበረ ቅዱሳን ሳይሆን በብዛት ለመረጣችሁ መምእመናን ስትሉ
የተመረጣችሁበትን ዋና አላማ አድርጋችሁ እኛ ምእመናኑ ደስ ብሎን ቅዳሴ ልቡን
ለእግዚአብሔር የሰጠ ቄስ (ባለፈው ስብሰባላይ ላይ ከልብ የሆነ ምስጋና በቅን ልቦናችሁ
ያፈሰሳችሁለት) አይነት ቄስ ፈልጋችሁ አምጡለን እንላለን።
በግልጽ ማህበረ ቅዱሳን መሆኑን አያሳየ በስድስት ዎር የቅስና ሹመት የተሰጠዉና መቅደስ ዉስጥ
ገብቶ የሚያበጣብጠዉን ቄስና ደጋፊዉን ዘባራቂ የእግዚአብሄር መልዕክተኛ አዎናባጅ
አስዎግዱልን እንላለን።
የጠየቅነው ጥያቄ እንዲፈጸምለን ለዓምላክ ከፍተኛ ጸሎት እናቀርባለን!!! ጸሎታችንንም
እንደሚሰማን አንጠራጠርም።
እስከተፈጸመልንም ድረስ በሰላም እንሰናበታችሁዋለን።
መልካም በአል ያድርግልን።
ደህና ሰንብቱ ብለን እዚህ ላይ እንዘጋለን።

Saturday, September 5, 2009

በቅርቡ አዲስ የምናዎጣውን ዜና እስትናቀርብ ድረስ ለናንተ ለቤተ ክርስቲያችን ተቆርቁዋሪዎች
የተከተለዉን የሃገር ፊቅር ራድዎ እንድታዳምጡ እንጋብዛለን፤
ይህ ሬድዮ ጣቢያ በኛ ቤተ ክርስቲያን ላይ የደረሰዉንና እየደረሰም የሚ
ገኘዉን የማሕበረ ቅዱሳን ተግባርና ግብ በግልጽ ያሳያል፤ በተለይም
የመጨረሻው ቁጥር 823 እና 830 ያዳምጡ፡
ላልሰማዉም ሁሉ ያዳርሱ እንላለን።


http://www.wmet1160.com/?page_id=136

Wednesday, August 26, 2009

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ርዕሰ አድባራት ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን አመሰራረቱ እና የአስተዳደር መዋቅሩ እንደሚከተለው ነው።

የዚህ ደብር ባለቤትና ዋና አካል የሆኑት የአባልነት ግዴታቸውን ያምዋሉ ምእመናን ሲሆኑ የእለት ተእለት አስተዳድራዊ ሥራዎች ደግሞ በመእምናኑ በተመረጡ ዘጠኝ የቦርድ አባላት ይከናወናሉ። እነዚህም ዘጠኝ የቦርድ አባላት ተጠሪነታቸው ለአባላቱ ነው።

ተጠሪነታቸው ለአስተዳደር ቦርድ የሆኑ የተለያዩ ንኡሳን ኮሚቴዎች በቦርዱ አማካኝነት ይቅዋቅዋማሉ፤ በቦርዱ አማካኝነትም ሊታጠፉ ይችላሉ።
የቦርድ አባላቱ የትመረጡበትን ኃላፊነት ለመወጣት በየአመቱ በፈረቃ እርስ በራሳቸው ተመራርጠውና የሥራ ድርሻ ተከፋፍለው ይሰራሉ።

ምሳሌ፡

ሊቀመንበር
ም/ሊቀመንበር
ዋና፡ ጸሐፊ
የሂሳብ ሹም
ገንዘብ ያዥ……ወዘተርፈ

በዚህ አይነት የሥራ ድልድል ካደረጉ በህዋላ የአስተዳደር ቦርድ አባላት እንደ አንድ ኮሚቴ በመሆን በአምላክና በምእመናን ፊት ቀርበው የገቡትን ቃል ኪዳን ለመፈጸም ይጥራሉ።

ሊቀመንበር ሆኖ የሚመረጠው ግለሰብ በቦርድና በአባላቱ የተላለፉትን ውሳኔዎች በሥራ ላይ መዋላቸውን እየተከታተለ ማስፈጸም ካልሆነ በስተቀር የፍጹማዊ አምባገነንነት ስልጣን የለውም። የአስተዳደር ቦርዱ አባላት ያላቸውን ሃሳብ በአጀንድ አስይዘው በቦርዱ ጉባኤ ላይ አቅርበው ተቀባይነትን ካገኘ ሃሳባቸው በሥራ የሚተረጎምበትን መንገድ ቦርዱ በህብረት ይፈልጋል። ካልሆነም ሃሳቡ ውድቅ ይሆናል።

ይህ ደብር ማንም የቦርድ አባል ከቦርድ ጉባኤ እና ከአባላት ምእመናን ጉባኤ ውሳኔ ውጭ የራሱን ሃሳብ እና ምኞት የሚያንጸባርቅበትና በሥራ ላይ ለማዋል ጫና የሚያደርግበት ቤተክርስቲያን አይደለም። ከዚህ አሠራር ውጭ የሚፈጸሙ ድርጊቶች በሙሉ በኃላፊነት ያስጠይቃሉ።
የባለአደራው የአስተዳደር ቦርድ ሥራውን ከላይ እንደተገለጸው በአግባቡ በመሥራት ላይ ይገኛል? ወይስ በግድ የለሽነት እየዳኸ ነው?
ይቀጥላል።
የቤተክርስቲያናችን አመሠራረትና አወቃቀር ለሚለው ጽሁፍ ተከታይ ሆኖ የቀረበ።

ቤተክርስቲያናችንን
ከቀበሌ የፍርድ ሸንጎ ወደ ተቀደሰ ደብር ለመለወጥ የተደረገ ጉዞ፡

ቀደም ሲል የዳላስ እና አካባቢው ምእመናን በአንድ ደብር ጥላ ሥር ተሰባስቦ ያመልክ ስለነበር የአባላት ቁጥር ከፍተኛ ነበር። ከአባላቱ የሚሰበሰበውም ብር ጠርቀም ያለ ነበር። ብር አዋጡ ተብለው ሲጠየቁ በኪሳቸው ውስጥ ያለውን እርግፍ አድርገው ሲሰጡ አይተናል። የዓይን ምስክሮችም ነን። የዚህ ደብር ምዕመናን ለአብነት የሚጠቀሱ ብዙ አኩሪ ሥራዎችን ሰርተዋል። ወርቃማ ታሪክ ያለው ትልቅ ደብር ነው። ዛሬ ግን ይህ ሁሉ ተረስቶ ቤተክርስቲያናችን በውጭና በውስጥ በክስ ተወጥራ ትገኛለች። ምዕመናን ተሰብስበው የሚያመልኩበት ሥፍራ መሆኑ ቀርቶ የቀበሌ የፍርድ ሸንጎ ካስመሰልነው ብዙ ዓመታት አስቆጥረናል። ያለው ችግር ተባብሶ እንዴት እዚህ ደረጃ ሊደረስ ቻለ?
በአጭር ጊዜ ውስጥ ተሰባስበን ከተጠበቀው በላይ አድገን ብዙ በጎ ሥራዎች እና ዕርዳታዎችን በሰፊው ሰጠን። ይህንን ፈጣን እድገት ከዳር ሆኖ ይመለከት የነበረው ወያኔ ሁለት ዕቅዶችን አውጥቶ ዘመተብን።
ዕቅድ አንድ ፤ ደብሩን በራሱ ቁጥጥር ሥር ማዋል።
ዕቅድ ሁለት ፤ ይህ ካልተሳካ ምዕመኑን መበተን እና ሀይሉን መስበር ናቸው።
እነዚህን ዕቅዶች ተግባራዊ ለማድረግ የዛሬ ስድስት ዓመት በተደረገው የቦርድ ምርጫ አባ ጳውሎስ እና ወያኔ በማህበረ ቅዱሳን አማካኝነት የቦርድ አባላትን አስመረጡ። ለረጅም ዘመን ምዕመናኑ ለልጆቻችን አስተማሪ ይቀጠርልን ብሎ ያቀረበውን ጥያቄ የተቀበ በማስመሰል በወቅቱ የነበረው ቦርድ የማህበረ ቅዱሳን መሪ የሆነውን ግለሰብ የቅዱስ ያሬድ ት/ቤት ኮኦርዲኔተር ብሎ ከቀጠረ በህዋላ ሕዝቡ ሳያውቅ በስውር “የቤተክርስቲያን አስተዳዳሪ” የሚል ሹመት ሰጡት።
በወቅቱ የነበሩት ርዕሰ ደብር ሞገስ እጅጉ እና መምህር ሰብስቤ ውሳኔው የነርሱን የሹመት ተዋረድ የሚጋፋ መሆኑን ሲረዱ ማህበረ ቅዱሳንን የሚቃውሙ መዘምራንን እና ምዕመናንን አሰባስበው መቅደስ ላይ በፈጠሩት እውከት ደብራችን ለሁለት ተከፈለ። ውስጥ ውስጡን በቀሳውስቱ፣ በማህበረ ቅዱሳን እና በተመራጭ የቦርድ አባላት መካከል ታምቆ የቆየው ቅራኔ ጊዜውን ጠብቆ ፈነዳ። ቤተክርስቲያናችን ችግር ላይ መውደቅዋም ይፋ ወጣ።
ርዕሰ ደብር በስማቸው ቀደም ብለው የቤተክርስቲያን ፍቃድ አውጥተው ዝግጅት ላይ መሆናቸውን ስንረዳ ምዕመናን አዘንን፣ ተቆጣን። ከመቶ ሰላሳ በላይ የምንሆን ምዕመናን ተሰብስበን ድርጊታቸውን አወገዝን፣ የመረጥነውንም ቦርድ መደገፍ እንዳለብን ተስማማን፤ በውስጣቸው አለመግባባትና ችግር ካለ ጉዳዩ በሥነ ሥርዓት መታየት አለበት እንጂ መቅደስ ላይ ሁከትን መፍጠር መፍትሄ ሊሆን እንደማይችል ገልፀን ለቦርዱ የድጋፍ ደብዳቤ አስገባን። ሌቦች ናችሁ፣ የቤተክርስቲያን ብር አባክናችሁአል፤ ከሥልጣን መውረድ አለባችሁ ተበለው ማጣፊያው አጥሮአቸው የነበሩትን የውቅቱን የቦርድ አባላት አረጋግተን ሥራቸውን እንዲቀጥሉ አደረግን።
ቦርድና ማህበረ ቅዱሳን ብር እያባከኑ ነው ብለው የተቃወሙ ወገኖች ራሳቸውን ከርዕሰ ደብር ለይተው ጥያቄአቸውን ማስረዳት ስለተሳናቸው ከቤተክርስቲያን ሲወጡ፤ በወቅቱ ውስጥ ለውስጥ ታምቆ የነበረውን ችግር በቅጡ ያልተረዳነው ወገኖች ቦርዱን አጠናክረን ከማህበረ ቅዱሳን ጋር ቤተክርስቲያን ቀረን።
ማህበረ ቅዱሳንም መድረኩን ተቆጣጥሮ ብቻውን በግላጭ መጋለብ ያዘ። የበጎ አድራጎትን ገንዘብ እንዳለ ተቆጣጠረ። ለድርጅቱ ፕሮጄክቶች ሥራ ማስፈጸሚያ ብር እንደፈለገ ያወጣ ጀመር፤ ታዋቂ መምህሮቻቸውን በየሦስት ወሩ ጉባኤ በሚል ሽፋን ወደ ዳላስ ማጉረፍ ጀመሩ። Video እና CD ቀርጸው ለአለም ማሰራጨት ጀመሩ። ለጉባኤ ከአዲስ አበባ ድረስ መምህራኖቻቸውን ማስመጣትን ሥራዬ ብለው ተያያዙ። ይህ ሁሉ የሚሠራው በደብራችን ገንዘብ ነበር።
ከዚህም በተጨማሪ በዚያኑ ሰሞን ባስቀጠሩአቸው ካህናቸው በኩል ያለቁርባን ጋብቻ እንደማይፈፀም አወጁ፤ ቀደም ብለን የተጋባነውንም ምዕመናን ዝሙተኞች መሆናችንን ማስተማር በሰፊው ተያያዙ። ይህንን ለመቕቕም ስንንቀሳቀስ ከማህበረ ቅዱሳን ጋር ግጭት ተፈጠረ። ይህንን አክራሪ ጥያቄያቸውንም እንዲያነሱ ተወሰነ። በሌላ በኩል የቤተክርስቲያን ሕግ ማሻሻያ (Amendment) አጥንታችሁ አቅርቡ ተብለው የተመረጡ ወገኖች፤ ሕጉን እንዳለ ለውጠው አዲስ ሕግ ይዘው ብቅ አሉ። ከነሱም ጋር ፍጥጫው ቀጠለ። ተንኮላቸውም ተኮላሸ።
የቦርድ አባላት ምርጫ ጊዜው ደርሶ ሲካሄድ፣ በማህበረ ቅዱሳን ቁጥጥር ሥር የነበረውን ቦርድ መለወጥ እንዳለብን አምነን ተነሳን።፡በተለይ ሁለተኛው ዙር የቦርድ ምርጫ ከተደረገ በሁአላ ማህበረ ቅዱሳን አድማ መምታትን ተቀዳሚ ሥራቸው አደረጉት። የቤተክርስቲያኑን ንዑሳን ኮሚቴዎች እኛ ካልተቆጣጠርን ለማንም አሳልፈን አንሰጥም አሉ። የደረሱበት፣ ያዩት፣ የነኩት በሙሉ የራሳቸው ይመስላቸዋል። በየቦታው ችግር መፍጠርን ሥራዬ ብለው ተያያዙ። የሥም ማጥፋት ዘመቻ፣ ሐሜት፣ ውሸት፣ ነገር ፈጥሮ ማውራት፣ ማስወራት የተካኑበት እንዲያውም እነርሱ የፈጠሩት እስከሚመስል ድረስ ተራቀውበት ለማየት ችለናል።
በወጣቶችና፣ በልጆች ፕሮግራም ውስጥ ማህበረ ቅዱሳን ካልሆነ ማንም ሊሳተፍ አይችልም በማለት ሽብር መንዛት ሥራዬ ብለው ተያያዙ። እሁድ አልፎ እሁድ ሲተካ ያለማቁአረጥ ረብሻቸውን አጥዋጥዋፉ። በአጠቃላይ ለቤተክርስቲያን ጉድይ ሳይሆን ጠባብ ለሆነው ለማህበራቸው ዓላማ መቆማቸውን እና ያላቸውን የዓላማ ፅናት በግልጥ በእውነት አየነው። ሆኖም ሥራቸውን እንደስማቸው ሙሉ ለሙሉ መንፈሳዊ ሆኖ አላገኘነውም። ይልቅስ በወጣትነታችን የምናውቀውን የፖለቲካ ድርጅት አስታወሱን።
ውድ ምዕመናን፤ ጠላቶቻችን ሊቆጣጠሩን፣ ካልሆነም ሊያፈርሱን እና ሊበታትኑን ያደረጉትን ሙከራ ከሞላ ጎደል ለመመልከት ችለናል። ለዚህ ሴራ በሩን ክፍት አድርገን ስለሰጠናቸው በዚያ ገብተው የሚፈልጉትን እየሠሩ ነው። ክፍት ሆኖ ያለው የጥፋት በርም የቤተክርስቲያኑ ልቅ የሆነና ቁጥጥር የሌለው የአስተዳደር ሥርዓት ነው። ላለፉት አሥራ ስምንት ዓመታት የተጠቀምንበት የአስተዳድር ስርአት ቤተክርስቲያናችን ልትወጣው የማትችለው አዙሪት ውስጥ ጨምሮአታል። በተሰበረና በማይሠራ ሥርዓት መልሰን ለመገልገል የሚደረገው ዕርምጃ መልሶ መላልሶ ስህተት ውስጥ ይጥለናል እንጂ አንድ እርምጃ ወደፊት አይወስደንም።
እኛ የኦርቶዶክስ አማኞች የምናውቀው ሚስጥረ ቤተክርስቲያን ሰባት ነው። የደብራችን ቦርድ ግን ስምንት ሚስጥራት አሉት። ሰባቱን ሚስጥራት አባቶች አስተምረውን አበጥረን እናውቃቸዋለን። ቦርዱ የፈጠረውን ተጨማሪ ሚስጥር ግን ምዕመናን አያውቁትም። ስምንተኝው ሚስጥር የቦርዱ አባላት ተመርጠው ሥራቸውን ሲጀምሩ መቅደስ ላይ በአባቶች ተባርከው ፀሎት ተደርጎላቸው ይሰናበታሉ። ከዚያ በሁአላ ጽሕፈት ቤት ውስጥ በር ዘግተው መጽሐፍ ቅዱስ ጨብጠው የሚሠሩትን ሥራ፤ የሚወስኑትን ማንኛውንም ውሳኔ፤ ሠራተኛ እንዴት እንደሚቀጥሩ፤ የቤተክርስቲያን ጥገናም ሆነ የተለያዩ ወጭዎችን በተመለከተ እርስ በራሳቸው ካልሆነ በስተቀር ለማንም እንዳይነግሩ ይማማላሉ።
እንግዲህ ቦርዱ ተጠሪነቱ ለመረጠው ሕዝብ መሆኑ ቀርቶ ተጠሪነታቸውን እርስ በራሳቸው አደረጉት። አሠራሩ በዚህ ዓይነት ለዘመናት የተዋቀረ ስለሆነ ደብራችን ዛሬ ያለችበት አስከፊ ችግር ውስጥ ልትወድቅ ችላለች።
በዚህ ምክንያት ይህን የመሳሰሉትን አስተዳደራዊ ችግሮችን ብንፈታ ዘላቂ ሠላምና መተማመን ይመጣል ብለን አሰብን። ግልፅ አሠራርን በቤተክርስቲያናችን ውስጥ መለማመድ አለብን ብለን ቆርጠን ተነሳን። በቅድሚያ መለወጥ ያለበት የሂሳብ አያያዝ ነው ብለን ወሰንን። ምክንያቱም ሕዝቡ ገንዘብ እንደሚባክን በይፋ መናገር ከጀመረ ቆይቶአል። የቀድሞ የቦርድ ተመራጮችን ሌቦች! ሌቦች! እያለ ያወገዘው በአደባባይ ነበር። እኛም ማህበረ ቅዱሳን የቤተክርስቲያኑን ገንዘብ ያለአግባብ ከተጠቀመባቸው መረጃዎች መካከል ጥቂቶቹን ለማየት ችለናል። ሂሳባቸውን ያላወራረዱ የቀድሞ የቦርድ አባላትን ሁሉ እናውቃለን። በ2006 ዓ/ም ቤተክርስቲያኑ ከ1.2 ሚሊዮን እስከ 1.5 ሚሊዮን ብር እንደነበረው በሰማንበት ጆሮአችን 2007 ወይም 2008 ላይ ያለው ብር አሽቆልቁሎ ስምንት መቶ ሺህ ብቻ እንደተቆጠረም ተነግሮናል። በምዋቹ በአቡነ ይስሐቅ ሥም በተከፈተው የባንክ ሂሳብ ውስጥ የነበረውም $450 ሺህ ብር በፍጥነት እንደተነነ ሰምተናል።
እነዚህን ሀቆች በመንተራስ አዲሱ የሂሳብ አሠራር ዘዴ ለቦርድ አባላት ቀረበ። የቀረበለትን አዲስ አሠራር መርምሮ በሥራ ላይ እንዲውል ከማድረግ ፈንታ የአስተዳደር ቦርዱ ይህንን ሀሳብ በጥንስሱ ማኮላሸት ፈለገ። ቀደም ሲል ከገንዘብ ጋር ንክኪ የነበራቸውን ሰዎች ሰብስበው የጋራ ግንባር ፈጠሩ። ይህን ሃሣብ ባቀረቡና ሃሣቡን በደገፉ የቦርድ አባላት ላይ የሥም ማጥፋት ዘመቻ አፋፋሙ። ሥማቸውን እየጠቀሱ በደረሱበት ቦታ ሁሉ የተመረጥንበትን ሥራ አላሠራ አሉን ብለው ማውራት ጀመሩ። ለስብሰባ ሲጠሩ አንመጣም እያሉ ያስቸግሩናል በማለት የሀሰት ወሬ መንዛት የዕለት ተዕለት ተግባራቸው ሆነ።
ቤተክርስቲያናችን ግልፅ የሆነ አስተዳደራዊ ሥርዓት መከተል አለባት ብለን የተነሳነውን ምዕመናን የደብራችን እንቅፋትና ችግር ፈጣሪዎች ናቸው፤ ምዕመናኑን እየበጠበጡት ነው፤ መመከር አለባቸው፤ ደብሩን ችግር ላይ ጥለውታል፤ ቤተክርስቲያናችን ውድቀት ላይ ያለችው በእነዚህ ግለሰቦች እና በከሳሾች ምክንያት ነው ብለው አወሩ። መፍትሔውም ሰላምና እርቅ የሚያመጣ ኮሚቴ መፍጠር ነው ብለው ተነስተዋል። እንግዲህ ፍርዱን ለአምላክና ለእናንተ ለምዕመናን እንተወዋለን። የቤተክርስቲያናችን የበላይ አካል አባላት ምዕመናን ናቸው። ቦርዱም ሥራውን ሪፖርት ማድረግ ያለበት ለምዕመናኑ ነው። የምዕመናኑንም ውሳኔ በሥራ ላይ ማዋል የቦርዱ ግዴታ ነው።
እሩቅ ሳንሄድ በዚህ በያዝነው ዓመት መጀመሪያ ላይ በተደረገው አጠቃላይ ጉባኤ የተላለፉት ውሳኔዎች ተፈጻሚነት አገኙ ወይ? ችግሩን የተለያየ ምክንያት በመፍጠር፤ ለምሳሌ፤ ፍርድ ቤት ስለተከሰስን ጌዜ ስጡን፤ ባይሎው እስከሚስተካከል ታገሱን በማለት የተመረጡበትን ሥራ በማግዋተትና የተወሰኑ ውሳኔዎችን እንክዋን በተግባር እንዳይተረጎሙና በስራ ላይ እንዳይውሉ አድርገዋል። ይህ ድርጊት ቤተክርስቲያኑን ከከሱት ግለሰቦች ይበልጥ እንደሆነ እንጂ አያንስም። ሕዝቡን ደግሞ ደጋግሞ ማሞኘት አይቻልም።
ውድ ምእመናን ስለ ግልጽ አሠራር (TRANSPARENCY) ለቦርዱ ያቀረብነው ጽሁፍ ከዚህ በፊት በድህረ ገጻችን ላይ ስላወጣን እንዳነበቡት ተስፋ እናደርጋለን። ካላነበቡትም “ጁን 16, 2009 ዓ/ም ስለመተዳደሪያ ደንብ ማሻሻያ ሃሳብ” ተብሎ የተጻፈውን ያንብቡ።

Saturday, August 22, 2009

አንደምን አደራቸሁ፣
ዛሬ ደግሞ ተኩላዎች የበግ ለምድ ለብሰዉ በመካከላችን ገብተው እንዲበጠብጡን አሁን ያለዉ
ቦርድ መልምሎ የቀጠረልን ቀሳዉስትና ዘማሪዎች በዋሸንግተን ዲሲ ያደረጉትን ስብሰባ ይመለከቱ ዘንድ ይህን ሊንክ ይክፈቱ.
እንደፈረንጅ አቆጣጠር ባዲሱ አመት መጀመርያ አጠቅላይ ጉባኣ
ላይ ስለ ማህበረ ቅዱሳን ያለፈዉን ዉሳኔ ቦርዱ በቦርዱ ዋና አላፊና ቦርዱ ዉስጥ
ባሉት ደጋፊዎቻቸው ተግባር ላይ እንዳይዉል እየተከላከሉ መሆናቸዉን ይረዱ።
ተግባር ላይ አንዲያዉሉ መጠየቅና ማስገደድ የያንዳንዱ አባላት መብት መሆኑን
አትዘንጉ።
ቦርዱ ባጭር ጊዜ ዉስጥ ይህን ጥያቄ ካላምዋላልን ኮቦርዱ ዉስጥ ማን ማን መሆናቸዉንና
ለምን የሚለዉን ጥያቄ ዘርዝረን እናቀርባለን።


http://www.mahiberekidusan.org/documents/MK%2011%20Tekelala%20Gubae/album/index.html

እንደተለመደው ኮፒ እና ፐስት አድርጉ.

Friday, August 21, 2009

ቤተክርስቲያናችንን የከሰሰው ቡድን ኦገስት 23 ቀን 2009 ዓ.ም. አባላቱ $20.00 ዶላር ስጦታ በመያዝ ተሰብስበው ስለክሱ ሪፖርት እንዲሰሙ ጋበዘ።
በሌላ በኩል ይህ ቡድን ኦገስት 19 ቀን 2009 ዓ.ም. በመልዕክተኞቹ በኩል ለቦርዱ ያቀረበው ቅድመ ዝግጅት ተቀባይነትን ካገኘ ቤተክርስቲያኑ ክሱን ለመከላከል ሲል ያወጣውን ወጭ ካሣ እንደሚከፍል ማሳወቁ ይታወሳል። እዚህ ላይ የራሳቸው ኪሣራ ሲታከልበት ወጭ የሚያደርጉት ገንዘብ ከፍተኛ እንደሚሆን ይጠበቃል። ሆኖም እኛ ቀደም ሲል የሰማነው ዜና ማህበረ ቅዱሳን እና ወያኔ ወጭያቸውን እንደሚሸፍኑ ነው። ይህ ሁሉ ብር እያለ $20.00 በስጦታ መልክ መሰበሰብን ምን አመጣው?
አብዛኛዎቹ ከሳሾች በተለያየ ወቅት የቦርድ አባል በመሆን ብር ያባከኑ እና ከማህበረ ቅዱሳን ጋር በማበር በበጎ አድራጎት ኮሚቴ ሥም ገንዘብ ሲዘርፉ የነበሩ ናቸው። ዛሬ ደግሞ ለየት ባለ መልክ አዲስ ዘዴ ቀይሰው ብቅ ብለዋል። ለእድምተኞቹ የእኛ ምክር ራሳችሁን ጠብቁ ነው። በከፋ ዘመን ዋለታችሁ ውስጥ ሊገቡ ነው የሚል ነው።
ከእናንተ አንዱ ክርስቲያን ከሆነው ወንድሙ ጋር ቢጣላ፣ ጉዳዩን የእግዚአብሔር ሰዎች በፍርድ እንዲያዩለት በማድረግ ፈንታ ለክስ ወደ አረማውያን የፍርድ ሸንጎ ለመሄድ እንዴት ይደፍራል? 1ኛ ቆሮ፡ 6፡1
ታዲያ አንድ ክርስቲያን ሌላውን ክርስቲያን ከሶ ወደ አረማውያን ፍርድ ቤት መውሰድ ይገባዋልን? 1ኛ ቆሮ፡ 6፡6
እውነትን በይፋ እናሳያለን

ኦገስት 18 ቀን 2009 ዓ.ም. ባቀረብነው ሪፖርት ላይ ከዘረዘርናቸው ሥሞች መሐከል አቶ በትሩ ገብረእግዚአብሔር በምሽቱ ስብሰባ ላይ አለመገኘታቸውን ሪፖርቱን ያነበቡ ምዕመናን ገልፀዋል። እኛም አቶ በትሩ ገብረእግዚአብሔርን ስለፈጸምነው ስህተት ይቅርታ እንጠይቃለን።
የአባ ጳውሎስ መልዕክተኛ ቡድን ኦገስት 19 ቀን 2009 ዓ.ም. ምሽት ላይ በድጋሚ ከቦርዱ ጋር ተሰብስቦ ነበር። በስብሰባው ላይ የተካፈሉ ቡድኖች፤
1፣ ከአዲስ አበባ የተላኩ ቆሞስ፤
2፣ ከአባ ጳውሎስ እና ከማህበረ ቅዱሳን ጋር በቅርብ የሚሠሩ ግለሰቦች፤
3፡ ስለቤተክርስቲያኑ ችግር የተሙዋላ መረጃ ሳይዙ የራሳቸውን የተደበቀ ዓላማ ለማስፈጸም ሽምግልና ውስጥ የገቡ ግለሰቦች ናቸው።
እነዚህ የአባ ጳውሎስ መልዕክተኞች ቦርዱ ቤተክርስቲያኑን የከሰሱ ሰዎች ክሳቸውን እንዲያነሱ ከፈለገ በቅድሚያ መፈጸም አለባቸው ብለው ያቀረቡትን ቅድመ ሁኔታ አስረድተዋል። ይኸውም ኤፕሪል ላይ የተሻሻለው (amended የሆነው) የቤተክርስቲያን ሕግ ተሽሮ የቀድሞው ሕግ እንዳለ በሥራ ላይ እንዲውል ነው።
ቦርዱ የቀድሞውን ሕግ መልሶ ሥራ ላይ ሲያውል ከሳሾችም ክሳቸውን እንደሚያነሱና ቤተክርስቲያኒቱ በዚህ ክስ ሳቢያ ያወጣችውን ወጭ ካሣ እንደሚከፍሉ የሚል ነበር።
ውድ አንባቢያን፤ ከዚህ ስብሰባ ላይ ይፋ ሆኖ የወጣ ነገር ቢኖር ቦርዱ ውስጥ ውስጡን ከአባ ጳውሎስ እና ከማህበረ ቅዱሳን ጋር እንደቀድሞው ተመልሶ ለመሥራት ደጅ ሲጠና መክረሙ ነው። ለዚህም ነው ከሳሾች እንድንመለስ ከፈለጋችሁ ሕጉን ወደ ቀድሞው ሥፍራ መልሱት ብለው መልዕክት የላኩባቸው።
ጃንዋሪ 2009 ዓ.ም. በተደረገው አጠቃላይ ስብሰባ ላይ ቤተክርስቲያናችን ገለልተኛ መሆኑዋ፣ ከማህበረ ቅዱሳንም ጋር እንደማንሠራ መወሰኑ አይዘነጋም።
ይህ የምዕመናን ውሳኔ ተግባራዊ ያልሆነበት ምክንያት አሁን ግልፅ እየሆነ ነው። ከቤተክርስቲያኑዋ አቁዋም ጋር ተፃራሪ የሆኑ ቀሳውስትን አቅፈው ደግፈው የምዕመኑን ቆሽት ማሣረር የዕለት ተዕለት ተግባራቸው ለምን እንዳደረጉት ልንገነዘብ ችለናል። የማህበረ ቅዱሳንን መምህራን እያስመጡ ማስተናገድ የጀመሩበት ምስጢር በዚህ ስብሰባ ምክንያት ግልፅ ሆኖ ወጥቶዋል።
እየመጣ ካለው አደጋ አምላክ ይጠብቀን።
ከከሀዲዎች ፍላፃ አምላክ ይታደገን

Thursday, August 20, 2009

በሰላም አሳድሮ በሰላም ያዋለንን አምላክ እያመሰገንን ለዛሬ ደግሞ
ይሀንን ሊንክ አናቀርባለን.

http://ethiomedia.com/adroit/yezare_sinodos.pdf

በደህና ያሳድረን.


አንደተለመደው ኮፕ አና ፐስት ያድርጉት

Wednesday, August 19, 2009

ለዛረ የሚከተለዉን (ሊንክ) ይክፈቱና ይመልከቱ.

http://ethiomedia.com/adroit/qumsina.pdf

ሊንኩን ለመክፈት ኮፒ ያድርጉና ብራዉዘሩ ላይ ፐስት ያድርጉ.

በሚቀጥለዉ ጊዘ እስንገናኝ

አምላክ ይጠብቀን

Tuesday, August 18, 2009

የሚቀጥለውን አድራሻ ይመልከቱ.


http://www.mahiberekidusan.org/Default.aspx?tabid=36&ctl=Details&mid=371&ItemID=236
ስአሉን ይጫኑ.

http://www.youtube.com/watch?v=SIDZpjwKTTk
እውነትን በይፋ እናሳያለን!!

ዘግይቶ የደረሰን ዜና

ሰሞኑን በአባ ጳውሎስ ደጋፊዎች ሰላምና እርቅ እየተባለ ሲቦካ የነበረው ሴራ ግቡን ይመታ ዘንድ ከአቡነ ጳውሎስ የተላኩት ልዩ መልእክተኛ እና የማህበረ ቅዱሳን በጅሮንድ ባለፈው እሁድ ሰንበት በቤተክርስቲያናችን በመገኘት ስለሰላምና እርቅ ሲሰብኩ መደመጣቸው ይታወሳል። እኚህ ደፋር መልእክተኛ ምእመናኑን ከቅዳሴ በሁዋላ ከቤተክርስቲያን እንዳይውጣ አዘው ካህናቱን እና ከሳሾችን አስክትለው ወደቦርድ ጽህፈት ቤት በመሄድ የቦርድ አባላትን ማነጋገራቸው እና ጉዳያቸውም ፈር እንደያዘ ለምእመናኑ ማሳወቃቸው አይዘነጋም። ይህ ድፍረታቸው ሲደንቀን ዛሬ ኦገስት 18 ቀን 2009 ዓ/ም ምሽት ላይ የቤተክርስቲያናችንን ከሳሾችና ግለስቦችን እንዲሁም የቦርዱን ሊቀመንበር ጨምረው በቤተክርስቲያናችን ውስጥ ሲዶልቱ አምሽተዋል።
ዋናው ጥያቄ የቦርዱ ሊቀመንበር የቦርድ አባላት ሳያውቁና ሳይፈቅዱ እኝህ አባት የማህበረ ቅዱሳን አባል እና የአባ ጳውሎስ ቆሞስ መሆናቸውን እያወቀ በተደጋጋሚ በቤተክርስቲያናችን ውስጥ እንደፈለጉ ገንዘብ እንዲሰበስቡ፤ ስብሰባ እንዲያካሄዱ እና ከከሳሾች ጋር አብረው እንዲዶልቱ የተባበረበትን ምክንያት ለሕዝቡ በአስቸክዋይ እንዲገልጽ እይጠየቅን በተጨማሪም በምንኖርበት ሀገር ሕግ መሠረት የተመስረተው ክስ ብያኔ ሳያገኝ፤ እንዲሁም ከሳሽ በተከሳሽ ቦታ ላይ መገኘት እንደማይገባው የሚያዘውን ሕግ ማስከበር (restraining order) ሲገባው በጎን ተደብቆ ከከሳሽ ጋር አብሮ መዶለት ለምን አስፈለገው? ይህ አድራጎቱ የግለስቡን ህቡዕ የተዛባና አወዛጋቢ አቅዋም ይፋ አውጥቶ እርቃኑን አስቀርቶታል።
በዚህ ስብስባ ላይ የተገኙ ግለሶቦች፤
1. ንቡረእድ (የአባ ጳውሎስ ቆሞስ)
2. አቶ ጌታቸው ወልደሚካኤል
3. አቶ በቀለ ተክሌ
4. አቶ መስፍን ወልደየስ
5. አቶ ኪዳኔ አለማየሁ (በቅርፍቡ የፍሎሪዳን ቤተክርስቲያን የበተኑ የአባ ጳውሎስ
ቀኝ እጅና የዳያስፖራ ቤተክርስቲያናት ብተና መሪ)
6. አቶ በትሩ ገብረእግዚአብሔር
7. ወ/ሮ ጥሩ አየር ፍስሀ
8. አቶ ኢዩኤል ነጋ እና ሌሎችም ግለሰቦች ይገኙበታል።